‹‹ጊዜ የጣለው ዛፍ ምሳር ይበዛበታል፤›› እንዲሉ የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ መሪ የነበሩት ኔልሰን ማንዴላ የቀድሞ የትዳር አጋር ኖምዛሞ ዊኒፍሬድ ዛንዩዌ ማዲኪዜላ ወይም በአጭሩ እንደሚጠሩት ዊኒ ማንዴላ፣ በደቡብ አፍሪካ የነበረውን የነጮች የግፍ አገዛዝ አፓርታይድን ለማጥፋት ካደረጉት ትግልና የቀድሞ ባለቤታቸው ኔልሰን ማንዴላ በእስር ላይ በነበሩበት ጊዜ ባለቤታቸውን ከማበረታታት አንስቶ የአፓርታይድ ትግሉን በማቀጣጠል ከነበራቸው ሚና ይልቅ፣ ነፃ የተባሉባቸውም ሆነ የተፈረዱባቸው የሙስና፣ የማጭበርበርና የግፍ ግድያዎች ክሶች በታሪካቸው ጎልተው ተጽፈዋል፡፡