Thu05172012

Go to :English Edition

Back Home

ከ41,000 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ ዕድል መፈጠሩ ተነገረ

  • PDF

በአማራ ክልል ባለፉት ስድስት ወራት ከ41,000 በላይ ዜጎችን የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የክልሉ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ልማት ኤጀንሲ ማስታወቁን ዋልታ ዘገበ፡፡

በግማሹ በበጀት ዓመቱ ከላይ ቁጥራቸው የተገለጸውን ሰዎች በአዲስ በማደራጀት፣ ነባሮችን በማጠናከርና በመንግሥት ትልልቅ ፕሮጀክቶች እንዲሳተፉ ሁኔታዎችን በማመቻቸት፣ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መቻሉን ዘገባው ያስረዳል፡፡

የሥራ ዕድሉ የተፈጠረላቸው በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣ በእንጨትና ብረታ ብረት፣ በከተማ ግብርና፣ በማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎትና በመንግሥት የግንባታ ፕሮጀክቶች አማካይነት መሆኑን ዘገባው ያስረዳል፡፡