| በስንዴ እጥረት 6ዐ ፋብሪካዎች ተዘጉ |
|
|
| Sunday, 23 March 2008 | |
|
ከስንዴ እጥረት ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ ካሉት 19ዐ ፋብሪካዎች መካከል 6ዐ ያህሉ ምርት ለማቆም መገደዳቸው ተገለፀ፡፡
የኢትዮጵያ ዱቄት አምራቾች ማህበር ሥራ አስፈፃሚና ፀሐፊ አቶ ጣሰው ኃይሌ ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለፁት ባለፉት ዓመታት ዱቄት አምራቾች በተለይ በግብዓት (ስንዴ) እጥረት መቸገራቸውን አስታውሰው በዚህም ምክንያት 6ዐ ያህሉ መዘጋታቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የስንዴ አቅርቦት ችግር መኖሩን ያስታወሱት አቶ ጣሰው ያሉት ሁለት የአርሲና የባሌ እርሻዎች የዘንድሮ ምርት ለመንግሥት አራትና አምስት ፋብሪካዎች ዓመታዊ ፍጆታ እንኳን የሚበቃ አይደለም" ብለዋል፡፡ (ዝርዝሩን በቆይታ አምድ ላይ ይመልከቱ) በጋዜጣው ሪፖርተር |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |