Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Thursday
Nov 20th
Home arrow Sections arrow ፌደራል ሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴርና...
ፌደራል ሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴርና... E-mail
Wednesday, 09 January 2008

ፌደራል ሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴርና ሲጂሲ ቻይና የ2000 ገልባጭ መኪናዎች ግዢ ስምምነት ተፈራረሙ

የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴርን በመወከል የተገጣጣሚ ህንፃ አካላት ማምረቻ ድርጅትና ሲጂሲ ኦቨር ሲስ ኮንስትራክሽን ኢትዮጵያ ሊሚትድ ከተባለ የቻይና ካምፖኒ ጋር የ2000 ገልባጭ መኪናዎች ግዢ ከትናንት በስቲያ ታህሳስ 25  2000 ዓ.ም ተፈራረሙ፡፡

የሥራና ከተማ ልማት  ሚኒስትር ዶ/ር ካሱ ኢላላ በስምምነቱ ወቅት እንደተናገሩት፣ መንግስት ከ400ሺ የማያንሱ የመኖሪያ ቤቶች /በኮንዶሚኒየም አይነት/ በአራት ዓመት ውስጥ ለመገንባት በያዘው ዕቅድ ለሲሚንቶ፣ አርማታ ብረትና የመፀዳጃ  ዕቃዎችን በፍጥነት ለማጓጓዝ በማቀድ የግዥ ስምምነቱን እንደተፈራረመ ተናግረዋል፡፡

ለፕሮግራሙ ስኬታማነት መንግስት ቅድሚያ በመስጠቱ አንድ ነጥብ ሁለት ሚሊዮን  ሲሚንቶ፣ ከ150ሺ የማያንስ የአርማታ ብረትና ቀሪውን የመፀዳጃ ቤት ዕቃዎች በውጭ ምንዛሪ በመግዛት ላይ መሆኑን ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡

በአንድ ጊዜ 40 ቶን እንደሚጭኑ የተነገረላቸው ተሽከርካሪዎች የሌሎች የንግድ እንቅስቃሴ ሳይጎዳ ለቤቶች ልማት ፕሮግራሙ የሚያገለግሉ የግል ትራንስፖርት ባለንብረቶች በባለቤትነት እንዲገዟቸውና የቀረቡላቸውን እቃዎች ባስተማማኝ እንዲያጓጉዙ ሁኔታዎች መመቻቸታቸውን ዶ/ር ካሱ ገልፀዋል፡፡

ስምምነቱን የተፈራረሙት የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴርን በመወከል የተገጣጣሚ ህንፃ አካላት ማምረቻ ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ከበደ ተሾመና የቻይና አምባሳደር ሚስተር ሊንሊን ሲሆኑ ሚኒስትሮችና አምባሳደሮችም ተገኝተዋል፡፡

በታምሩ ጽጌ

Last Updated ( Wednesday, 09 January 2008 )
 
< Prev   Next >