Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 06th
Home arrow Sections arrow ለኢትዮጵያ ተደራዳሪዎች ስልጠና ሊሰጥ ነው
ለኢትዮጵያ ተደራዳሪዎች ስልጠና ሊሰጥ ነው Print E-mail
Sunday, 23 March 2008
የዓለም የንግድ ድርጅት ለኢትዮጵያን ተደራዳሪዎችና የንግድ ባለሙያዎች አባልነቱ ለታደጊና ላላደጉ አገራት የሚኖረውን ጠቀሜታ በሚመለከት ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ስልጠና ሊካሄድ ነው፡፡

ስልጠናው ከመጋቢት 22 ቀን እስከ 26 2000 ዓ.ም በሲዊዘርላንድ ጄኔቫ የሚካሄድ ሲሆን የወርክሾፑ አላማ ኢትዮጵያ ለዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ የቡድኑ ስለሚያደርገው ሂደት ማሳወቅ ነው፡፡

ስምምነቱ ለማድረግ ስለሚያግዙ ስትራቴጂዎች፣ ትኩረት በሚሰጣቸው ዘርፎች ዙሪያ ውይይት ይካሄዳል የስልጠናው ተሳታፊዎች በግብርናና በአገልግሎት ዘርፍ ስለሚካሄዱ ስምምነቶችና በንግድ ሂደት አስፈላጊ የሆኑ መመሪያዎችን እንዲያውቁ ያስችላል፡፡

በአገልግሎት ዘርፍ ለመደራደር የሚያስችል አቅም እንዲያዳብሩ እንደሚያስችላቸውም ተገል"ል፡፡

ስልጠናው ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት መስፈርቶችን እንድታሟላና በብሔራዊ ደረጃ አስፈላጊ የሆኑ የልማት አማራጮችን እንድታይ እገዛ እንደሚያደርግ ታምኖበታል፡፡ 
 
< Prev   Next >