| ዕድሮች የሸማቾች ሕብረት ሥራ... |
|
|
| Sunday, 23 March 2008 | |
|
ዕድሮች የሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበር ለማቋቋም እየተንቀሳቀሱ ነው
በአዲስ አበባ አስተዳደር በተለያዩ ቀበሌዎች የሚገኙ ዕድሮች የሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበር ለማቋቋም የሚያስችላቸውን እንቅስቃሴ በማከናወን ላይ መሆናቸውን አቶ መለሰ ተካ የአዲስ አበባ ዕድሮች ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ ገለፁ፡፡ እስካሁንም ባካሄዱት እንቅስቃሴ የሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበርን አስመልክቶ ለዕድር አባላቱ የግንዛቤ ማጎልበቻ ትምህርት በመስጠትና አስፈላጊውን ቅስቀሳ በማድረግ ላይ መሆናቸውን ምክትል ሊቀመንበሩ አስረድተዋል፡፡ የሸማቾች ሕብረት ሥራ ማህበር በሚቋቋምበት ጊዜ በአቅም ውስንነት ሳቢያ አክሲዮን መግዛት ለማይችሉ የዕድሩ አባላት የየዕድሩ ምክር ቤቶች በስማቸው የአክሲዮን ዕጣ እንደሚገዙላቸውና አባላቱም በረጅም ጊዜ ክፍያ ዕዳቸውን ለመሸፈን የሚያስችላቸው ሁኔታ እንደሚመቻችላቸው አቶ መለሰ አስታውቀዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በየቀበሌውና በአስሩም ክፍለ ከተሞች የዕድሮች ምክር ቤቶች መቋቋማቸውን አቶ መለስ አመልክተው የክፍለ ከተሞቹ ዕድር ምክር ቤቶች ደግሞ በአዲስ አበባ አስተዳደር የጋራ መድረክ መፍጠራቸውን ገልጸዋል፡፡ እነዚሁ ምክር ቤቶችም በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ የደም ልገሳ እንዲካሄድ በማድረግ፣ በኤች አይ ቪ/ኤድስና በሌላም ሳቢያ ወላጅ አልባ የሆኑ ሕፃናትን በመንከባከብና በአጠቃላይ በኤች አይ ቪ ዙሪያ ግንዛቤ በማስጨበጥ ትምህርት በመስጠት የሚደነቅ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ኃላፊው አመላክተዋል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |