Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Friday
May 09th
Home arrow Sections arrow የቲቢ በሽታን ለመቆጣጠር በወጣው...
የቲቢ በሽታን ለመቆጣጠር በወጣው... Print E-mail
Sunday, 23 March 2008
የቲቢ በሽታን ለመቆጣጠር በወጣው ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ክትትል እየተደረገበት ነው

ከመላ ሀገሪቱ በሚሌኒየሙ የቲቢ በሽታን ሥርጭት ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣው የእቅድ አፈጻጸም ላይ ያተኰረ ክትትል በመካሄድ ላይ መሆኑን ዶክተር ዘሪሁን ታደሰ በጤና ጥበቃ ሚኒስትር የበሽታዎች መከላከያና መቆጣጠሪያ መምሪያ ኃላፊ አስታወቁ፡፡

ክትትሉን የሚያደርጉትም የፌዴራል ጤና ጥበቃ፣ የክልል ጤና ቢሮ ኃላፊዎችና በተዋረድ ያሉ ሌሎች ኃላፊዎች መሆናቸውን ኃላፊው አስረድተዋል፡፡

የፌዴራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የቲቢ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ከፍተኛ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ኃላፊው አመልክተው ከተከናወኑትም ተግባራት መካከል ሕብረተሰቡ ስለ ቲቢ በሽታ ያለውን ግንዛቤ በማሳደግ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ማስቻል አንዱ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ዘንድሮ የሚከበረውም የዓለም የቲቢ ቀን አከባበር ይህንን ዓለማ በሚያግዝ መልኩ እንዲሆን መታቀዱን፣ ዕለቱም በዓለም ደረጃ "አይ አም ስቶፒንግ ቲቢ" እና በአገር አቅፍ ደረጃ ደግሞ "የጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኞች ለቲቢ በሽታ መከላከልና መቆጣጠር ቁልፍ ሚና አላቸው፡፡" በሚል መርህ ሀሳብ የሚከበር መሆኑን ዶ/ር ዘሪሁን  ተናግረዋል፡፡
 
< Prev   Next >