Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 11th
Home arrow Sections arrow አውሮፕላን ውስጥ ሞባይል ስልክ መጠቀም ተፈቀደ
አውሮፕላን ውስጥ ሞባይል ስልክ መጠቀም ተፈቀደ Print E-mail
Wednesday, 26 March 2008
የዱባይ አየር መንገድ ቅርንጫፍ የሆነው የኢምሬትስ አየር መንገድ ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳፋሪዎች አውሮፕላን ውስጥ የሞባይል ስልካቸውን እንዲጠቀሙ ፈቅዷል፡፡
አየር መንገዱ የሞባይል ጥሪ አውሮፕላን ውስጥ እንዲቀበሉ ለተሳፋሪዎች ፈቃድ የሰጠው ከዱባይ እስከ ካዛብላንካ ባለው መስመር ነው፡፡ በተለያዩ አውሮፕላኖች ውስጥ ሲስተሙን ለመዘርጋት እቅድ መያዙንም አየር መንገዱ አመልክቷል፡፡

ተሳፋሪዎች የሞባይል ጥሪ መቀበል የሚችሉበት ጊዜም ተወስኖላቸዋል፡፡ አውሮፕላኑ መደበኛ በሆነ ፍጥነት እየበረረ ባለበት ወቅት ሞባይል ማናገር የሚፈቀድላቸው ሲሆን የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ሲስተሙ ጥቅም ላይ ሲውል መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል፡፡

ጥሪ ከመቀበል በተጨማሪ ተሳፋሪዎቹ የፅሁፍ መልዕክቶችን መላክ እንደሚችሉ ተገል..ል፡፡ በማታ በረራ የሚደረጉ የስልክ ጥሪዎችን ግን የአውሮፕላኑ ሠራተኞች መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል፡፡ የስልክ ጥሪዎችን ለመቀበል ሞባይሎቻቸው ድመፅ የሚያሰሙበት ሙድ ላይ (silent mood) ላይ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡

ከዚህ በፊት አውሮፕላን ውስጥ የሞባይል ጥሪ መቀበል የሚከለከለው ከአውሮፕላኑ የድምፅ መልዕክት ማስተላለፊያ ሲስተም ጋር እንዳይጋጭ ነበር፡፡ ኤሮ ሞባይል በተባለው ኩባንያ ተሰርቶ የተዘጋጀውና በኢምሬትስ አየር መንገድ ጥቅም ላይ የዋለው ሲስተም ሞባይሉም ሆነ የአውሮፕላኑ ሲስተም ሳይጋጩ ሥራ ላይ እንዲውሉ የሚያስችል ነው፡፡ ሲስተሙ ሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት ግን አየር መንገዱ ከዓለም አቀፍ የአየር መንገድ ደህንነት ድርጅት ፈቃድ ማግኘት ይኖርበታል፡፡

የኢምሬት አየር መንገድ በዱባይ መንግሥት ስር የሚተዳደር ሲሆን 60 ወደሚደርሱ ሀገራት ይበርራል፡፡
 
< Prev   Next >