Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Friday
Aug 29th
Home arrow Sections arrow በቴዲ አፍሮ ክስ የምስክሮችን...
በቴዲ አፍሮ ክስ የምስክሮችን... Print E-mail
Sunday, 30 March 2008
Imageበቴዲ አፍሮ ክስ የምስክሮችን ቃል ፍ/ቤት አዳመጠ

ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) “ሰለሜ” በሚለው የሙዚቃ አልበሙ የፈጠራ ሥራዬ የሆኑ ሥዕሎቼን ከፍቃዴና ከዕውቅናዬ ውጪ ተጠቅሟል በሚል ከቀረበበት የወንጀል ክስ ጋር በተያያዘ ፍ/ቤት የዐቃቤ ሕግ ሁለት ምስክሮች ቃል አዳመጠ፡፡

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 10ኛ ወንጀል ችሎት ባለፈው ዓርብ ዕለት ዐቃቤ ሕግ ያቀረባቸውን ሁለት ግለሰቦች ምስክርነት አዳምጠ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ፍ/ቤቱ በቀጣይ ቀጠሮው የዐቃቤ ሕግን በክሱ ላይ ያቀረበውን ማስረጃ መርምሮ ቴዲ አፍሮን ይከላከል ወይም መከላከል ሳያስፈልገው በነፃ ይሰናበት የሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ቴዲ አፍሮ በሰለሜ አልበሙ ሲዲ ውስጥ የፈጠራ ሥራዬን ከዕውቅናዬ ውጪ ተጠቅሟል በሚል የፈጠራው ሥራ ባለቤት ነኝ በሚሉ አቶ አዲስ ገብሩ ተከስሶ በዚህ ጉዳይ ፍ/ቤት ሲቀርብ ይህ ለሦስተኛ ጊዜ መሆኑ ታውቋል፡፡

በጋዜጣው ሪፖርተር
 
< Prev   Next >