| ቴሌና ተጠቃሚዎች በሲም ካርድ... |
|
|
| Sunday, 30 March 2008 | |
|
ቴሌና ተጠቃሚዎች በሲም ካርድ አቅርቦት ጉዳይ አልተስማሙም
የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን በበቂ ሁኔታ የሞባይል ሲም ካርድ ማቅረብ ባለመቻሉ መቸገራቸውን ተጠቃሚዎች ገለፁ፡፡ ቴሌ የሲም ካርድ አቅርቦት ችግር እንደሌለ አስታውቋል፡፡ አገልግሎት የተጓደለባቸው ተጠቃሚዎች ለሪፖርተር ጋዜጣ እንዳስታወቁት ኮርፖሬሽኑ የሲም ካርድ ችግር እንደሌለ በተደጋጋሚ ቢገልፅም ገበያ ላይ ማግኘት አልቻሉም፡፡ የሞባይል ስልክ አስፈላጊ በሆነበት በአሁኑ ወቅት ኮርፖሬሽኑ የተጠቃሚዎችን ፍላጐት ማርካት አለመቻሉ ቅር እንዳሰኛቸው የገለፁት አገልግሎት ጠያቂዎች “ኮርፖሬሽኑ አስቸኳይ መፍትሄ ሊሰጠን ይገባል” ብለዋል፡፡ የተገልጋዮች አቤቱታን አስመልክቶ ኮርፖሬሽኑ እንዳስታወቀው ችግሩ የሞባይል ሲም ካርድ ሳይሆን በክልል ከተሞች ያለው የኔትወርክ አቅም አለመሟላት ነው፡፡ ቀደም ሲል ለክልሎች የተገነባው አቅም የማስፋፊያ ሥራ ስላልተሰራለት ከአዲስ አበባ ሲም ካርድ የሚገዙ ተገልጋዮች ወደ ክልል እየወሰዱ መጨናነቅ በመፍጠራቸው ሳቢያ በአዲስ አበባ ሲም ካርድ ሽያጭ እንዲቆም መደረጉን፣ ሽያጩ እንዲቆም የተደረገውም ለጊዜው እንደሆነ ኮርፖሬሽኑ አስታውቋል፡፡ በቬንደር ፋይናንሲንግ ከተገኘው ገንዘብ ውስጥ 5.6 ሚሊዮን የሞባይል ደንበኞችን ማስተናገድ የሚያስችል ስምምነት ከዜድ ቲ ኢ ኩባንያ ጋር በየደረጃው መደረጉን ኮርፖሬሽኑ ገል..ል፡፡ በዚሁ መሠረት 1.2 ሚሊዮን ደንበኞችን ለማስተናገድ ታስቦ በሚሌኒየም ፕሮጀክቱ በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ እቅዱ ተግባራዊ መሆኑን ያመለከተው ኮርፖሬሽኑ 4.4 ሚሊዮን ደንበኞችን ለማስተናገድ በተመረጡ 15 የክልልና የንግድ ማዕከል በሆኑ ከተሞች የኔትወርክ ማስፋፊያ ሥራ መጀመሩን ገል..ል፡፡ የሦስተኛው ትውልድ (ዘመናዊ አገልግሎቶች) መስጠት የሚያስችል 250 ሺ የሞባይል ሲም ካርድ ተዘጋጅቶ የሙከራ ሥራው ተጠናቆ በርክክብ ላይ መሆኑን፣ 250 ሺ የገመድ አልባ ስልክ ሲም ካርድም በተመሳሳይ መልኩ ለተጠቃሚው ለማድረስ ዝግጅቱ መጠናቀቁን ኮርፖሬሽኑ አስታውቋል፡፡ በአሰግድ ተፈራ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |