Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Thursday
Aug 07th
Home arrow Sections arrow ስኳር ከውጪ ተገዝቶ መግባት ይጀምራል
ስኳር ከውጪ ተገዝቶ መግባት ይጀምራል Print E-mail
Sunday, 30 March 2008
Image
አቶ ግርማ ብሩ
የፓልም ዘይት ከታክስ ነፃ ተደረገ

የኑሮ ውድነቱን ለመቀነስ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከትላንትና ጀምሮ የፓልም ዘይትን ሙሉ በሙሉ ከታክስ ነጻ ሲያደርግ የልብስ ሳሙና ላይ ተጥሎ የነበረው ሱር ታክስ እንዲነሳ አድርጓል፡፡ የስኳር ፍላጎት ላይ እጥረት እንዳይከሰት 1.5 ሚሊዮን ኩንታል ስኳር ወደ አገር ውስጥ ይገባል፡፡
የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አቶ ግርማ ብሩ አርብ ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የፓልም ዘይት ሙሉ በሙሉ ከታክስ ነፃ መደረጉን፣ በደረቅና በዱቄት የልብስ ሳሙና ላይ ተጥሎ የነበረው የሱር ታክስ ከትላንት ጀምሮ መነሳቱን አስታውቀዋል፡፡

አቶ ግርማ ብሩ በመጪው የክረምት ወራት ምክንያት የስኳር ምርት እጥረት እንዳይከሰት ሲባል ከውጭ አገር 1.5 ሚሊዮን ኩንታል ስኳር ግዢ እንደሚፈጸም ገልጸዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ አራት መቶ ሺ ኩንታል ስኳር ግዢ የጨረታ ስርዓቱ ተጠናቆ በመጪው ሚያዚያ ወር ወደ አገር ውስጥ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ ቀሪው 1.1 ሚሊዮን ኩንታል ስኳር በሚቀጥለው አርብ በሚከፈተው የጨረታ ስነስርዓት ግዢው ይፈፀማል፡፡

መንግሥት የዘይት ዋጋ ንረትን ለመቀነስ 10 ሚሊዮን ሊትር ዘይት ገዝቶ በጅንአድና በሌሎች የጅምላ አከፋፋይ ነጋዴዎች አማካኝነት ያሰራጫል፡፡ መንግሥት የፓልም ዘይትን ሙሉ በሙሉ ከታክስ ነፃ በማድረጉ ከ4 እስከ 5 ሚሊዮን ብር የታክስ ገቢ እንደሚያጣ አስታውቀዋል፡፡

ከዚህ ባሻገር በእህል ገበያው ከማረጋጋት አንፃር ገብስና ማሽላ ወደ ውጭ እንዳይላኩ መከልከሉን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡  

በተሾመ ንቁ
 
< Prev   Next >