| በአዲስ አበባ ለ52 ድርጅቶችና... |
|
|
| Sunday, 30 March 2008 | |
|
በአዲስ አበባ ለ52 ድርጅቶችና ግለሰቦች መሬት ተፈቀደ
ከቀጣይ ወር የአካባቢና የማሟያ ምርጫ በኋላ የሚሰናበተው የአዲስ አበባ ከተማ ጊዜያዊ ባለአደራ አስተዳደር ከመስከረም እስከ የካቲት 2000 ዓ.ም. ድረስ መሬት እንዲሰጣቸው የተወሰነላቸውን 52 ያህል ድርጅቶችና ግለሰቦች ስም ዝርዝር ይፋ አደረገ፡፡ የአስተዳደሩ መሬት ልማትና አስተዳደር ቦርድ መሬት እንዲሰጣቸው ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ ጊዜያት ወሰነላቸው ባለጉዳዮች መካከል የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኀበር ከሊዝ ነፃ በአራዳ ክፍለ ከተማ 286 ካሬ ሜትር ቦታ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ በቦሌ ክፍለ ከተማ በካሬ ሜትር 287.45 ብር ሂሳብ 5ዐ ሺ ካሬ ሜትር ቦታ፣ የአፍሪካ ኀብረት ለሆቴል ግንባታ የሚውል ከሊዝ ነፃ 118 ሺ 827 ካሬ ሜትር ቦታ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ፣ የአዲስ አበባ ንግድና የዘርፍ ማኀበራት ምክር ቤት ለዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን ማዕከል ግንባታ የሚውል ከሊዝ ነፃ 110 ሺ 126 ካሬ ሜትር ቦታ በቦሌ ክፍለ ከተማ እንዲወስዱ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ የሊዝ ቦርዱ መሬት ከፈቀደላቸው ግለሰቦች መካከል ሼህ ኤልያስ ሬድዋን የኢትዮጵያ እስልምና ጠቅላይ ጉባዔ ምክትል ሊቀመንበር በቦሌ ክፍለ ከተማ 500 ካሬ ሜትር ቦታ በካሬ ሜትር ብር 559.80 ሒሳብ እንደተፈቀደላቸው ይጠቁማል፡፡ የአስተዳደሩ ሊዝ ቦርድ መሬት ለማግኘት ካመለከቱ በርካታ ድርጅቶችና ግለሰቦች መካከል “ተፈቅዶላቸዋል” በሚል የዘረዘራቸው የተመረጡበት መስፈርት ምን እንደሆነ የጠቀሰው ነገር የለም፡፡ አስተዳደሩ የስም ዝርዝራቸው የተጠቀሱት ግለሰቦችና ድርጅቶች ቀርበው ውል እንዲፈፅሙ አሳስቧል፡፡ በጋዜጣው ሪፖርተር |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |