|
Sunday, 30 March 2008 |
|
የኢትዮጵያ ሠራተኞቸ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን 200 የሚደርሱ የአገር ውስጥና የውጭ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት የንግድ ትርዒት ሊያካሄድ ነው፡፡
የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለፁት የንግድ ትርዒቱ የሚካሄደው የዘንድሮውን የሜይዴይ በዓል ምክንያት በማድረግ ነው፡፡ የንግድ ትርዒቱ በሚሌኒየም አዳራሽ ከሚያዚያ 13 እስከ 23 ቀን 2000 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡
ከንግድ ትርዒቱ የሚገኘው ገቢ ኮንፌዴሬሽኑ በደብረዘይት ከተማ ግንባታው ለተጀመረው የአበራ ገሙ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን ማሰልጠኛ ተቋም ወጪ ይውላል፡፡
ማዕከሉ ቀደም ብሎ ተይዞ በነበረ ግምት 31 ሚሊዮን ብር ይፈጃል ተብሎ የነበረ ሲሆን አሁን ግን ከዚህ በላይ ይሆናል ተብሎ ይታሰባል፡፡
የማዕከሉ ግንባታ በሶስት ፌዝ የሚከናወን ሲሆን በመጀመሪያውና በሁለተኛው ፌዝ የሠራተኛ መሪዎች እና የሙያ ማሰልጠኛ ሕንፃዎች ግንባታ የሚያጠቃልል ሲሆን በሦስተኛው ፌዝ የኮሌጅ ግንባታ ይከናወናል፡፡ በአሁኑ ወቅት በቦታው ላይ የመሰሰቢያ አዳራሽ ተገንብቶበታል፡፡ በዳዊት ታዬ |