Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 06th
Home arrow Sections arrow በሕገወጥ የውጪ ምንዛሬ የተሰማሩ...
በሕገወጥ የውጪ ምንዛሬ የተሰማሩ... Print E-mail
Wednesday, 02 April 2008
በሕገወጥ የውጪ ምንዛሬ የተሰማሩ ንግድ ፈቃዳቸው ታገደ

በሕገወጥ ምንዛሬ ተሰማርተዋል ተብለው የተያዙ የንግድ ፈቃዳቸው መታገዱን የየክፍለ ከተሞቹ የንግድ ኢንዱስትሪ ጽህፈት ቤቶች አስታወቁ፡፡

ለግለሰቦቹ የተፃፈው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ለእግዱ ምክንያት የሆነው የንግድ የሥራ ፈቃድ ከተሰጠበት አላማ ውጭ ሲገለገሉና ተገቢ ያልሆነ ሕገወጥ የንግድ ሥራ ሲሰሩ መገኘታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በማረጋገጡ ነው፡፡

"ስለሆነም" ይላል ደንበኛው "ስለሆነም በንግድ ምዝገባና ፈቃድ አዋጅ ቁጥር 67/89 አንቀጽ 26 ንዑስ አንቀጽ ሐ መሰረት ንግድ ፈቃዱም እንዲታገድ የተወሰነ መሆኑን እናስታውቃለን"

የየክፍለ ከተሞቹ ደንብ ማስከበር ትዕዛዙን ተቀብለው ደብዳቤው ከደረሰ ጊዜ ጀምሮ የንግድ ሥራቸውን እንዲያቆሙ ማስጠንቀቂያ ጽፏል፡፡

በዚህ የእግድ ማዘዣ ኢትዮጵያ ሆቴል አካባቢ፣ ጋንዲ ሆስፒታል አካባቢ፣ ካዛንቺስ፣ ሂልተን ጀርባና መርካቶ አካባቢ በሕገወጥ ምንዛሬ ስራ ተሰማርተዋል ተብለው የተከሰሱ ድርጅቶች ይዘጋሉ፡፡  

በጋዜጣው ሪፖርተር
 
< Prev   Next >