Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow በፑንትላንድ የኢትዮጵያ ወታደሮች...
በፑንትላንድ የኢትዮጵያ ወታደሮች... Print E-mail
Sunday, 06 April 2008
በፑንትላንድ የኢትዮጵያ ወታደሮች አለመኖራቸው ፕሬዚዳንቱ አስተባበሉ

የኢትዮጵያ ወታደሮች አንፃራዊ መረጋጋት ባለበት የፑንትላንድ ግዛት ውስጥ ሰፍረዋል የሚል ግምት የክልሉ ፕሬዚዳንት ማስተባላቸው ጋሬዋይ አንላይን ዘገበ፡፡

የክልሉ ፕሬዚዳንት መሐመድ “አዴ” ሙሴ ይህንን ያሉት ባለፈው እሁድ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው በፊት በቦሳሰ የወደብ ከተማ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ነው፡፡

ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት ወደ አዲስ አበባ ያደረጉት ጉዞ ክልላቸው ከኢትዮጵያ ያላት ኢኮኖሚያዊና የፀጥታ ግንኙነት ለማጠናከር መሆኑን ነው፡፡

የክልሉ ፕሬዚዳንት የኢትዮጵያ ወታደሮች በፑንትላንድ ግዛት ውስጥ በውጭ ኩባንያዎች ሊካሄድ የሚችል የነዳጅ ኢንቨስትመንት ለመከልከል በአካባቢው ሰፍረዋል የሚል አሉባልታ አስተባብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ወታደራዊ የልዑካን ቡድን ባለፈው ወር በፑንትላንድ ዋና ከተማ ከነዳጅ ኩባንያው ተወካዮችና ከክልሉ የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር የዝግ ስብሰባ ማድረጋቸው ድረ ገፁ ገል..ል፡፡

በጋዜጣው ሪፖርተር
 
< Prev   Next >