Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow ሴቶች ጥሩ የፋይናንስ....
ሴቶች ጥሩ የፋይናንስ.... Print E-mail
Sunday, 06 April 2008
ሴቶች ጥሩ የፋይናንስ መሪ መሆን አልቻሉም

በፋይናንስ የትምህርት ዘርፍ በመማር ላይ ያሉ ሴት ተማሪዎች ቁጥር በርካታ ቢሆንም ትምህርታቸውን አጠናቀው በሙያቸው ከፍተኛ ደረጃ ላይ የመድረስ እድላቸው ግን አነስተኛ መሆኑን የሚያሳይ ጥናት ረቡዕ እለት ይፋ ሆነ፡፡
 
በቻርተርድ ሰርቲፋይድ አካውንታንት ማኅበር የተካሄደው ጥናት፣ ከሴቶች ይልቅ ለወንዶች የፋይናንስ ምሩቃን የመሪነት አቅም ቀላል እንደሆነ ስልሳ ሦስት በመቶ የሚሆኑ የፋይናንስ አመራሮችን ጠቅሶ አመልክቷል፡፡

ጥናቱ በ3381 የማኅበሩ አባላት ላይ የተደረገ ሲሆን ኢትዮጵያን ጨምሮ ከመቶ አሥራ ስድስት አገሮች ከተውጣጡ 19 የፋይናንስ ሴት አመራሮች ቃለ መጠይቅ ተደርጎላቸዋል፡፡ ይህ በሴቶቹ ብቃት ማነስ ሳይሆን በሥራ ሕይወታቸው ሚዛናዊነት ምክንያት እንደሚከሰት ጥናቱ ቢጠቁምም ይህ ነው የሚባልና የሚጎላ ምክንያት አልተጠቀመም፡፡

የተቋማዊ የተሳሳተ እይታና ባህላዊ ተጽዕኖዎች ጎልተው በምክንያትነት ተቀምጠዋል፡፡ ባለፉት አስርት ዓመታት ችግሩ የሥራ መስኩና ችግርና በመስኩ የተሰማሩ ሴቶች ጥረት አለማድረግ መሆኑ ጐልቶ ቢገለጽም ባህላዊ ተጽዕኖዎች ሴቶች ላይ የሚያደርሱት ተጽዕኖም ትልቁ ምክንያት እንደሆነ ተገልጿል፡፡
 
< Prev   Next >