Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Friday
Aug 29th
Home arrow Sections arrow በ27 ሚሊዮን ብር ለሚገነባው....
በ27 ሚሊዮን ብር ለሚገነባው.... Print E-mail
Sunday, 06 April 2008
በ27 ሚሊዮን ብር ለሚገነባው ቤተመጻሕፍት ማሰሪያ የሚውል ቦታ እስካሁን አልተገኘም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሚሌኒየም ጽህፈት ቤት በ27 ሚሊዮን ብር ወጪ ለሚያቋቁመው የሕዝብ ቤተመጻሕፍት ሕንፃ መገንቢያ የሚውል ቦታ በማፈላለግ ላይ መሆኑን የጽህፈት ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኪሮስ ኃይለሥላሴ አስታወቁ፡፡

 

ሕንፃውን ለመገንባት ታስቦ የነበረው በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል አጠገብ በሚገኘውና በግ ተራ አካባቢ ባለው ቦታ ላይ እንደነበር አቶ ኪሮስ አመልክተው፣ ይኸው ቦታ ለኢንተርናሽናል ሆቴል ግንባታ እንዲውል በመደረጉ ሌላ ቦታ የማፈላለጉ እንቅስቃሴ መቀጠሉን አስረድተዋል፡፡

የሕንፃው ዲዛይን በ350ሺህ ብር ወጪ ተሰርቶ እንደተጠናቀቀ፣ የሕንፃው ግንባታ ሲያልቅምቱ የአካል ጉዳተዮችንና ሕፃናትን ጨምሮ ለኅብረተሰቡ የተሟላ የንባብ አገልግሎት የመስጠት አቅም እንደሚኖረው አቶ ኪሮስ አስታውቀዋል፡፡

 
< Prev   Next >