Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow ክቡር ሚኒስትር
ክቡር ሚኒስትር Print E-mail
Wednesday, 09 January 2008
- ክቡር ሚኒስትር እውነቱን እንናገር ከተባለ የሚያስንቁን እርስዎ ነዎት
- እንዴት?
- ፀረ ሕዝብ የሆነን ሃይል እናጥራው እንቀይረው ስንል እርስዎ ቆዩ፣ ረጋ በሉ፣ ሰው እንዳይጎዳ ተጠንቀቁ እያሉ መስሪያ ቤቱ የሌቦች መፈንጫ ሆነ፡፡
- አስተውሉ አልኩ እንጂ አታጥሩ አትስሩ አልኩ?
- ክቡር ሚኒስትር እርምጃ በወቅቱና በቦታው ካልተወሰደ ምን ዋጋ አለው? አልሰራም ያለ መባረር አለበት፡፡

- አልሰራም ብለሃል ውጣ ማለት ቀላል ነው፡፡ ነገር ግን ሠራተኛው ደግሞ አላሰራ አሉኝ ብሎ እየወቀሰ ነው፡፡
- ውሸት ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡ የሚሰራውማ እየተሻለው ነው፡፡ ይልቁንስ አላሰራ ያሉኝ እኔን ነው፡፡
- እሺ መወሰድ አለበት ስለምትለው እርምጃ አጥንተህ አቅርብልኝ፡፡
- አመሰግናለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡ እንደ ኤክስፐርትና እንደ አማካሪ አጥንተህ አቅርብልኝ ሲሉኝ ሞራሌ ከፍ ይላል የሥራ ፍላጎቴም ይነሳሳል፡፡
- ገና ላየው ነው እንጂ አፀደቅኩት ማለት እኮ አይደለም፡፡
- ካዩትማ እንሚያፀድቁት እርግጠኛ ነኝ፤ በሙያዬ እተማመናለሁ፡፡
- ከአሁን በፊት አጥንተህ ያቀረብክልኝ መቼ ትክክለኛ ነበሩና?
- የትኞቹ ክቡር ሚኒስትር?
- ሁለት ሶስቱ ጥናቶችኮ የተበላሹ ነበሩ፡፡
- ያ ሌባ ነዋ..
- የትኛው ሌባ?
- ከእኛ መሥሪያ ቤት ወጥቶ አሁን የራሱን የከፈተው፡፡
- እሱ ምን አደረገ?
- እኔ በኮምፒውተር ፃፈው ብዬ ስሰጠው ያልሆነ ነገር አስገብቶበት ነዋ፡፡
- በል በል አሁን አጥናና አቅርብልኝ፡፡
- እሺ፡፡
ረከሳምንት በኋላ ክቡር ሚኒስትሩ ወደ ውጭ መሄድ ነበረባቸውና ወደ አውሮፕላን ማረፊ እየሄዱ ነው፡፡ አማካሪያቸው ደወለ፡፡ ሾፌራቸው ስልኩን ሰጣቸውሪ
- እሺ ምን ሆንክ?
- ክቡር ሚኒስትር ወደውጭ ከመሄድዎ በፊት ጥናቱን አይተው ይፈርሙልኝ፡፡
- አሁን ኤርፖርት እየሄድኩ ስለሆነ የት ሆኜ ነው የማጸድቀው?
- ችግር የለም፡፡ እኔ እዚያው ኤርፖርት ነኝ፡፡
- ስደርስ እንነጋገራለን፡፡ ቻው፡፡
ረሾፌራቸው ራሱን ያካልሪ
- ምን ሆነህ ነው?
- ክቡር ሚኒስትር ይቅርታ ያድርጉልኝ በማይመለከትህ ገባህ አይበሉኝ እና አንድ ነገር ልናገር፡፡
- ተናገር፡፡
- ይህ አማካሪ የተባለው በሚያቀርብልዎ ሰነድ ላይ ባይፈርሙ ጥሩ ነው፡፡
- ለምን?
- ሰራተኛው ሁሉ ይጠላዋል፡፡
- ለምን ይጠላዋል፡፡
- ዋና አጭበርባሪና ሌባ ነው ይለዋል ደግሞም ያወራል፡፡
- ምን ብሎ ነው የሚያወራው?
- እኔ ባልኖር ኖሮ ይህ መሥሪያ ቤት ገደል ይገባ ነበር ይላል፡፡
- ሌባ የሚሉትስ ለምንድን ነው?
- ያቺን ሆቴል ካቋቋመ ወዲህ ሌባ ይሉታል፡፡
-  ሆቴል አቋቋመ እንዴ?
- ትንሽ ናት እንጂ አዎን፡፡
- እም... ከእሱ ጋር ትንሽ ላውራ፡፡ አንተ ሻንጣውን አስገባልኝ፡፡
- እሺ ክቡር ሚኒስትር፡፡
ረከአማካሪያቸው ጋር ያወራሉሪ
- ጥናቱ ይኸው ክቡር ሚኒስትር፡፡ ተግባር ላይ ይዋል ብለው ይፈርሙልኝ፡፡
- ሳላነበው እንዴት ነው የምፈርመው? ለአንድ ሳምንት ነው የምሄደው ስመለስ እፈርመዋለሁ፡፡
- ክቡር ሚኒስትር ማጠናከሪያ እርምጃችሁን ላኩልን ብለውን የለ፡፡ በሁለት ቀን ውስጥ መቅረብ አለበት፡፡ የማጠናከሪያ ሃሳብና እርምጃ የለንም ብለን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ማቅረብ ውርደት አይሆንም?
- አላነበብኩትም ብየኮ ነው፡፡
- እኔና እርስዎ አብረን ስንሰራኮ ታላቁ ጸጋ እርስ በርስ መናበባችን ነው አያምኑኝም ማለት ነው?
- ማመንማ አምንሃለሁ፡፡
- እኔም እርስዎን አምኘ ነው እንጂ ስኮላርሺፕ አግኝቼ እንደነበር ያውቃሉ፡፡
- አውቃለሁ፡፡ እሺ በል አምጣው፡፡ ይኸው ፊርማ ማለት ይህ ነው አይደል? ደስ አለህ?
- ስለፈረሙልኝ አመሰግናለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
- የመግቢያ ሰዓት ደርሷል፡፡ ቻው፡፡
- የሰላም መንገድ ክቡር ሚኒስትር፡፡
- ቻው፡፡
ረክቡር ሚኒስትር ከሳምንት በኋላ ተመለሱ፡፡ መሥሪያ ቤቱ ብጥብጥ ብሏል፡፡ ፀሐፊያቸውን ይጠይቃሉሪ
- አንቺ ምን ሆኖ ነው ይህ መሥሪያ ቤት? ሰዎች ስልክ እየደወሉ አንድ ነገር አድርግ እያሉኝ ናቸው፡፡
- አማካሪ ኤክስፐርት ተብዬው በጥብጦ ነዋ፡፡
- እንዴት?
- ሌቦቹ ተሸፋፍነው ደህና ደህና ሰዎች አባረራችሁ፡፡
- ሾፌሩኮ በቀደም አስጠንቅቆኝ ነበር አልሰማ ብዬ ነው እንጂ፡፡
- የትኛው ሾፌር?
- የእኔው ሾፌር ነዋ፡፡
- ሌባ ነው፡፡ ጫት ከማመላለስ ሌላ እሱ ደግሞ ምን ያውቃል? እኔ ሁልጊዜ እፈራለሁ፡፡
- ምን ሆነሽ ነው የምትፈሪው?
- እሱ እንዴት የእርስዎ ሾፌር ይሆናል ብዬ ነዋ፡፡
- እሺ በኋላ እናወራለን፡፡ አሁን የሞቀ ቡና ላኪልኝ፡፡
- እሺ ክቡር ሚኒስትር፡፡
- ማን ናት ያቺ ቆንጆ ቡና ለምታመጣልኝ ልጅ ንገሪያት፡፡
- እሺ ክቡር ሚኒስትር፡፡
ረፀሀፊዋ ወጣች፤ ቡና አቅራቢዋ ገባችሪ
- እኔኮ ያንቺን ቡና ነው የምወደው፡፡
- አመሰግናለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
- ሆን ብዬኮ አንቺ እንድታመጪ ለፀሐፊዬ ነግሬ ነው፡፡
- አውቃለሁ እርስዎ እንደዚያ ባይሉማ እሷ አትጠራኝም፡፡
- ለምን?
- እሷ እዚህ መሥሪያ ቤት ውስጥ ቅባቶች፣ ልብሶችና ሌሎችም ዕቃዎች ትሸጣለች፡፡ የሚኒስትሩን ቢሮ ሱቅ አታድርጊው ስላልኳት ትጠላኛለች፡፡
- ህ... ም
ረሰራተኛዋ ወጣች ፀሐፊዋ ገባችሪ
- ክቡር ሚኒስትር ቅሬታችንን ማሰማት እንፈልጋለን የሚሉ ሰራተኞች አሉ ላስገባቸው?
- ቡና አቅራቢዋም ቅሬታ አላት፡፡ ታውቂ ነበር?
- ይህች ሌባ፡፡
- ማን  ሌባ?
- አሁን ቡና ያቀረበችው፡፡
- እንዴት ሌባ ሆነች?
- የመስሪያ ቤቱን ሳሙና ወደ ቤትዋ ትወስዳለች፡፡
- እስቲ አስተዳዳሪውን ጥሪልኝ፡፡
- የትኛውን አስተዳዳሪ?
- የአስተዳደር ኃላፊውን ነዋ፡፡
- አማካሪው ልኮታል፡፡
- የት?
- አብረው ሆቴል እየሰሩ አይደል፡፡ የሚያስገቡት ዕቃ አለ መሰለኝ
- ምክትሉን ጥሪልኝ፡፡
- ምክትሉማ ከተባበሩት አንዱ ነው፡፡
- በይ ያቺ ማን ናት ስሟን ጥሪልኝ፡፡
- ያችን አጋሰስ ማለትዎ እንዳይሆን?
- ኧረ ተይ ጥሩ ሰው ናት፡፡
- ጅል ናት፡፡
- በቃ ተይው ሌላ ጊዜ ይሁን፡፡
- እና እነዚህ ቅሬታ አለን የሚሉት አስገቢያቸው፡፡
- ይግቡ፡፡
ረገቡሪ
- ምን ነበር?
- አቤት ክቡር ሚኒስትር፡፡
- ቅሬታ አላችሁ? ልትናገሩ ነው የመጣችሁት መሰለኝ?
- እኛ ቅሬታ የለንም ክቡር ሚኒስትር፡፡
- ቅሬታ የላችሁም? አላግባብ ተቀጣን፣ አልተስማማንም የምትሉት ነገር የለም?
- እኛ አልተስማማንም፣ ደህንነትም አልጠራንም፣ አልተቀጣንምም? 
- ታዲያ ለምን መጣችሁ?
- ክቡር ሚኒስትሩ ሊያናግሩዋችሁ ይፈልጋሉ ተብለን ነውኮ የመጣነው፡፡
- ይቅርታ ሂዱ ሌላ ጊዜ እጠራችኋለሁ፡፡ የክፍል ኃላፊያችሁን አነጋግራለሁ፡፡
- ያንን ሌባ፡፡
- እንዴት?
- ክቡር ሚኒስትር እሱን ከሚያነጋግሩ ዝም ቢሉ ይሻላል፡፡
- ለምን?
- እሱኮ ደላላ ነው፡፡ ቢሮም አይገባም፣ ሲደልል ነው የሚውለው፡፡ ስለ እሱ ብዙ አናውቅም፣ እሱም ስለእኛ ብዙ አያውቅም፡፡
- ማነው ሂዱና ተናገሩ ወይም ሚኒስትሩ ያነጋግሯችኋል ያላችሁ?
- የፋይናንስ ኃላፊው፡፡ ለነገሩ ሰውየው የራሱ ችግር አለበት፡፡
- የምን ችግር?
- ከእርስዎ አማካሪ ጋር ጥለኛ ናቸው፡፡ አማካሪውን እንድንወቅስለት ይፈልጋል፡፡ ለዚህ መሰለን የላከን?
- አማካሪው መጥፎ ነው  እንድትናገሩ?
- አማካሪውምኮ ሌባ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡ ሁለት ዝሆኖች ሲጣሉ ሳሩ ይጎዳል ብለን እኛ እነሱ መሃል አንገባም፡፡
- አማካሪውን የምትጠሉት ለምንድነው?
- አንጠላውም፡፡ እኛንም ይጠቅመናል፡፡ ሆቴሉን ሲያሰራ ቅዳሜና እሑድ ያሰራን ነበር፡፡ ጥሩ ከፍሎናል፡፡ አሁን ሆቴሉን ሲሸጠውም ገዢ ፈልጉ ብሎ ጠቁሞናል፡፡
- ሆቴሉ ተሸጠ እንዴ?
- ትናንት ሸጠው፡፡
- ለምን?
 ውጭ አገር ሊሄድ ፈልጓል መሰለኝ፡፡
- እሺ ቻው፡፡
ረፀሐፊያቸው ጋር ደወሉረሪሪ
-  ኦዲተሩን  ጥሪልኝ፡፡
- የለም፡፡
- እንዴት የለም?
- ተባሯል እኮ፡፡ በእርስዎ አማካሪ ከተባረሩት አንዱ ነው፡፡
- ለምን?
- ገንዘብ ሰርቀሃል፣ አላወራረድክም ብሎ አማካሪውን ወጥሮ ስለያዘው አባረረው፡፡
- እስቲ   ጥሪልኝ፡፡
- የለም፡፡
- የት
- አልገባም?
- ትናንት ገብቶ ነበር?
- ትናንትማ  ነበር፡፡ እርስዎም አልገቡም ነበር፡፡ አራት ቀኑ ነው፡፡
- እንደው እስቲ ቤቱ ደውይልኝ፡፡
- ደውዬ ነበር፡፡ ውጭ አገር ሄዷል አለችኝ ሠራተኛው፡፡
- አመንሻት?
- እሷን ሳይሆን እዚህ ሰራተኞች ሲያወሩ ሰምቼ አመንኩ፡፡
- የሰማሽው ምንድነው?
- ትናንት ውጭ አገር ሆኖ በሬዲዮ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
- ምን የሚል መግለጫ?
- ከአገር የወጣበትን ምክንያትና ሥራውን የለቀቀበት ምክንያት፡፡
- ምክንያቱ ምንድነው አለ?
- መስሪያ ቤቱ አላሰራ ስላለኝ ነው፡ አለ፡፡
- እሱም?

 

 
< Prev   Next >