Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 20th
Home
ያለፈውን ምርጫ፡- Print E-mail
Wednesday, 09 April 2008
ጠንካራ ጎን እናጠናክር፤ ደካማ ጎን እናስወግድ!

በአንድ አገር የምርጫ ታሪክ ልዩ ትኩረትና ክብደት ሊሰጠው የሚገባ በምርጫው ማን አሸነፈ የሚለው ሳይሆን ምርጫው እንዴት ተካሄደ እንዴት ተከናወነ የሚለው ነው፡፡ ምክንያቱም የምርጫ ሂደት የሥርዓት ነፀብራቅ ሲሆን አሸናፊ ፓርቲ ግን በየጊዜው ሊቀያየር ይችላል፡፡ የምርጫ ሥርዓት ዘላቂነት ያለው ሲሆን ተመራጭ ፓርቲ ግን የወቅቱ ፖለቲካዊ ሁኔታ ነፀብራቅ ሊሆን ይችላል፡፡

በአገራችን በኢትዮጵያም መመዘኛችኝ ይኸው ነው፡፡ የምርጫ አካሄዳችን እንዴት ነበር የሚለው ነው፡፡ ያለፈው የ1997 ዓ.ም ምርጫችን ከምርጫው በኋላ ተበላሸ እንጂ የሚያኮራና ዴሞክራሲያዊ ሂደት ነበረው፡፡ ከነግድፈቱም ቢሆን የአገራችንን የምርጫ ታሪክና ሂደት አንድ ትልቅ እርምጃ ወደፊት ተራምዷል፡፡

ያለፈው ምርጫችን ልንማርበት የሚገባና ልናጠናክረውና ልናስወግደው የሚገባ ሁለት ምዕራፎች የያዘ ነበር፡፡

እስከ ምርጫው ዕለት የነበረው ምዕራፍ በዋነኛነት በአዎንታ የሚገለፅ አኩሪ ምዕራፍ ነበር፡፡ በርካታ ፓርቲዎች ለውድድር የተሰለፉበት ከፍተኛ ቅስቀሳ በመላው አገራቱ የተካሄደበት ነበር፡፡ የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ሰፊ የክርክር መድረክ ያዘጋጁበትና ያስተላለፉበት ነበር፡፡ በርካታ ሕዝብ ለምርጫ የተመዘገበበትና በከፍተኛ ስነ ሥርዓት እስከሌሊት ድረስ የመረጠበት ነበር፡፡ እጅግ ሰላማዊና ደማቅና አዎንታዊ መንፈስ ያዘለ ምርጫ ነበር፡፡ የመጀመሪያው የምርጫ ውጤት ሲነገር እንኳ ተቃዋሚዎች በአዲስ አበባ ሙሉ በሙሉ አሸነፉ የሚል ነበር፡፡

ከላይ የጠቃቀስናቸው በቀላሉ ሊታይና ሊገመት የሚገባው አይደለም፡፡ ልናዳብረው የሚገባ የምርጫ ሂደታችንን ጠንካራ ጎን ነው፡፡

ሆኖም ከምርጫው በኋላ አሉታዊ ተሞክሮዎችም በብዛት ታይተውበታል፡፡ ጥቂቶችን እንጠቃቅስ፡፡ ገና ምርጫው ሳይነገርና ሳይቆጠር ብቻ ሳይሆን በአንዳንድ አካባቢ ገና ሕዝቡ መረጦ ሳይጨርስም ምርጫው ተጭበርብሯል፣ የሚል አስፈላጊ ያልሆነ  መግለጫ ተሰጥቷል፡፡ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሳያሳውቅ ውጤቱን ተወዳዳሪዎች ገልፀዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ንትርክ ተከስቷል፡፡ አብሮ የተወዳደረ የተቃዋሚ ጎራ ተሰነጣጥቋል፡፡ በኢትዮጵያዊያን ከማመን ይልቅ በውጭ ታዛቢዎች ላይ መተማመን ተጀመረ፡፡ የውጭ በተለይም የአውሮፓ ታዛቢዎች ከስነ ሥርዓትና ከስነ ምግባር ውጭ መግለጫ ሰጡ፡፡ እስከ ምርጫው ዝግጅትና ዕለት በጭራሽ ያልታየ የፀጥታና የደህንነት ሃይል ወደ መድረክ መውጣት ጀመረ፡፡ አላስፈላጊና ዘረኛ ቅስቀሳ ሕዝብን መከፋፈል ጀመረ፡፡ ግድያ እስር ሆነ፡፡

ከምርጫ በኋላ የታየው የጠቃቀስነው ሁኔታ በአሉታ የሚጠቀስ በቀጣይ የፓርቲ ሂደት በጭራሽ ሊደገም የማይገባ ነው፡፡

እንግዲያውስ ስለ ቀጣይ ምርጫ ሰታሰብ ጠንካራ ጎንን የሚያጠናክር ደካማ ጎንን የሚያስወግድ ምርጫ መሆን እንዳለበት ማረጋገጥ ነው፡፡ ዋናው ቁም ነገርም ነፃና ዴሞክራሲያዊ የምርጫ ሁኔታ መፍጠርና አሉታዊና እርስ በርስ የሚያጋጭ ዘረኛ ቅስቃሳ ማስወገድ፣ ከዛም ወደ ግድያ፣ እስርና ይቅርታና መፈታት የሚያመራ አላስፈላጊ ነገር ሁሉ ማስወገድ አስፈላጊ ነው፡፡

ይህ የሁሉም ወገን ሃላፊነት ነው፡፡ የገዥው ፓርቲ የተቃዋሚ ፓርቲና የሕዝብ ሃላፊነት ነው፡፡

ገዥው ፓርቲ በዚህ ምርጫ ያለፈው ስህተት እንዳይደገም ምን ላድረግ? ያለፈውን ጠንካራ ጎን ይበልጥ ለማጎልበት ምን ልስራ? ብሎ ማሰብና ከልብ መንቀሳቀስ ይኖርበታል፡፡

የተቃዋሚ ፓርቲዎችም እንደዚሁ ባለፈው ምርጫ ምን ፈፀምን? ምን ስህተት ነበረብን? ምን ልናስወግደው የሚገባ ነገር አለ? ብለው ራሳቸውን መገምገም ይኖርባቸዋል፡፡ ተስተካክለው ሊቀርቡ ይገባል፡፡

ሕዝብም ቢሆን ሁሉም ነገር ለእነሱ መተው የለበትም፡፡ ሕዝብ ራሱ የሚጠቀመውን ለይቶ ማወቅ ይኖርበታል፡፡ በትክክል ሊያይና ሊከታተል ይገባል፡፡ አዎንታዊ ቅስቀሳ እንደ አሉታዊ ቅስቀሳ እንዳይቀበል በውል ማሳወቅና ግልፅ መልዕክት ለፓርቲዎች ሊያስተላልፍ ይገባል፡፡

የማሟያ ምርጫ ለማካሄድ በመጨረሻ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን፡፡ ለአዲስ አበባ ምክር ቤትም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ምርጫ እያካሄድን ነው፡፡ ለአዲስ አበባ በሙሉና ለተወካዮች ምክር ቤት በጎደሉት፡፡

ይህ የምርጫ ሂደት ተጨማሪ አዎንታዊ ተሞክሮ የምንሰንቅበት መድረክ አድርገን ልንጠቀምበት ይገባል፡፡ በዚህ ተሞክሮ ለቀጣይ ዋና ምርጫ የተጠናከረ ዝግጅት የምናደርግበት ይሆናል፡፡

በዚህ የማሟያ ምርጫ ባለፈው ምርጫ ያገኘናቸው አዎንታዊ ተሞክሮዎች አጠናክረን አሉታዊ ተሞክሮዎችን አስወግደን የተሻለ የአዲስ አበባ ምክር ቤትና የተሻለ ፓርላማ ይዘን የምንጓዝበት መሆን ይገባናል፡፡

በዚህ የማሟያ ምርጫ የምንጠብቀው አንድ ዓብይ እርምጃ የተገኘውን ውጤት ማንኛውም ወገን በደስታ አሜን ብሎ እንዲቀበለው ነው፡፡ ምርጫና ሁከት አብሮ ይሄዳሉ የሚል በአፍሪካ እየተያ ያለው ገፅታ መቀየር አለብን፡፡ በአፍሪካም ምርጫን በደስታ መቀበል ተጀምሩዋል፤ የሚል መልዕክት ማስተላለፍ ይጠበቅብናል፡፡

ይህንና ይህን ስናደርግ ነው ያለፈው ምርጫ አዎንታዊ ገፅታ አጎልብተን ደካማ ገፅታውን ወደ አዎንታዊ ተሞክሮ ልንለውጠው የምንችለው፡፡ ከተሞክሮ ውጭ ልንጠቀም የምንችለው፡፡
 
< Prev   Next >
Headline
  • Pause
  • Previous
  • Next
1/10
Image የመናፈሻው ባለቤት ማነው?
በብሔራዊ ቤተመንግስት ምስራቅና፣ ከአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ምዕራብ እያዋሰነ እስከ ታላቁ ቤተ መንግስት የሚደርሰውና ለሕዝብ ክፍት ሆኖ የኖረው መናፈሻ   ማናቸውም ዜጋ እንዳይገለገልበት ዝግ ሆኖ ቆይቷል፡፡

Read more...
 
 
Politics
ከእኛ በላይ ስለኛ ማንም ሊናገር አይችልም!
እንደሚታወቀው ሁሉ አምባገነኑ የደርግ መንግስት በመጣል ለሰላም፣ ለፍትህ፣ ለዴሞክራሲና ለብሄር ብሄረሰቦች መብት መከበር የተካሄደው የትጥቅ ትግል ለድል የበቃል በመላው ህዝባችን ተሳትፎና በጠራ መስመር የሚመራ አላማ መሆኑ ፀሐይ የሞቀው አገር ያወቀው ሃቅ ነው፡፡ የታገልንለት ህዝባዊ መሰረት ያለው አላማም የታጋዩን የመላው ኅብረተሰብ የአላማ ጽናትና አይበገሬነት በተግባር ያስመሰከረ፣ ለአረመኔው የደርግ ስርዓትና ጋሻጃግሬዎቹ እንደ እግር እሳት እያንገበገበ ህዝባዊ ቀንዲልን ያወገገ ታሪካዊ ፍጻሜ እንደሆነም ሁሉም የሚመሰክርለት ጉዳይ መሆኑ አንድና ሁለት የለውም፡፡

Briefs
በእንስሳት ማድለብ ሥራ 1ዐ...

በእንስሳት ማድለብ ሥራ 1ዐ ሚሊዮን ብር ትርፍ ተገኘ

በትግራይ ማዕከላዊ ዞን ስምንት ወረዳዎች በእንስሳት ማድለብ ሥራ የተሰማሩ አርሶ አደሮች አስር ሚሊዮን ብር ትርፍ ማግኘታቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

 

 
Business & Economy
Image የሆላንድ ካርን ድርሻ ለመግዛት...
የሆላንድ ካርን ድርሻ ለመግዛት የቻይና ኩባንያ እየተደራደረ ነው

ከ370 በላይ የሚሆኑ አባይ አውቶሞቢሎች ተሸጡ

በዳዊት ታዬ

Shemach
ለተወደደው ኑሮ መፍትሄ ምን?
በናታን ዳዊት

ወቅታዊው የምግብ እህል እጥረትና የኑሮ ውድነት አለም አቀፋዊ ይዘት እንዳለው ሰምተናል፡፡ በምግብ እጥረትና በኑሮ ውድነት ዙሪያ የሚሰራጩ ዓለም አቀፍ መረጃዎችም ይህንኑ ይጠቁማል፡፡ ከምግብ እጥረት ጋር ተያይዞ የተፈጠረው የዋጋ ንረት እንደ ኢትዮጵያ ያሉ አገራትን በጣም እየጎዳ መሆኑን እያንዳንዳችን ማስረጃ ልንሆን እንችላለን፡፡

 
Interview
Image "ካለን ውስን የሰው ኃይል፣ ፋይናንስና...
"ካለን ውስን የሰው ኃይል፣ ፋይናንስና ጊዜ አንጻር ትልቅ ሥራ አከናውነናል"
አቶ ቴዎድሮስ ዘውዴ
የአዲስ አበባ ከተማ ሚሌኒየም ጽ/ቤት ምክትል ዳይሬክተር

አቶ ቴዎድሮስ ዘውዴ የአዲስ አበባ ከተማ ሚሌኒየም ጽ/ቤት ምክትል ዳይሬክተር ናቸው፡፡ ጽ/ቤቱ የተቋቋመበትን ተግባር ለማጠናቀቅ ሁለት ወራት ብቻ በቀ ረበት በዚህ ወቅት ከጽ/ቤቱ የሥራ ክንውን ጋር በተያያዘ ፍሬው አበበ አነጋግሯቸዋል፡፡

Fermata
አማን በአማን
ከከባድ እንቅልፍ ሰውን ለመቀስቀስ
ከጥንታዊ ክብሩ ዳግም ለመመለስ
ቢነሣ ሶክራቲስ ቢወለድ ኢየሱስ፤
እነ ስም አይጠሩ
ሳይፈሩ ሳያፍሩ
 
Kibur Minister
ክቡር ሚኒስትር

(ሚኒስትር መሥሪያ ቤት በኃላፊነት እንዲያሳካ የተሰጠውን ፕሮጀክት የሚገመግም ከአገር ውስጥና ከውጭ የተውጣጣ የኤክስፐርቶች ቡድን ክቡር ሚኒስትሩ መሥሪያ ቤት ድረስ መጥቷል፡፡ እሳቸውም ከባለሙያዎቻቸው ጋር ናቸው፤ ስብሰባው ተጀምሯል)

 

Life & Art
Image ጀግኖቻችንን ለማክበር

በሔኖክ ያሬድ

በኢትዮጵያ ከስም የዋለ ተግባር ያከናወኑ ምርጥ ሰዎች መኖራቸው፣ ማለፋቸው የተመዘገበ ነው፡፡ በጀግንነትም ይጠቀሳሉ፡፡ ከሰብዓዊ ጥናት በተለይም በኪነ ጥበባት ዘርፍ አንቱ የተባሉ ኢትዮጵያውያን የመኖራቸውን ያህል በጦር ውሎ የተወደሱት ጀግኖች ያህል ክብር የተሰጣቸው ምን ያህል እንደሆኑ እምብዛም አይታወቅም፡፡

 

 
Social
Image "ጃንጥላና ሹራብ ሰሪ ክረምት ይወዳል"

በምህረት አስቻለው

መርካቶ ራጉኤል ቤተክርስቲያን አቅራቢያ ከሚገኝ አንድ የልብስ ሱቅ ደጃፍ ላይ የተበላሹ ጃንጥላዎችን ሲጠግኑ አገኘኋቸው፡፡ አቶ አራርሳ ሔርጶ ለሃያ ዓመታት በእሳት አደጋ መከላከያ ብርጌድ ውስጥ በጥበቃነት፣ በአደጋ ተከላካይነት እንደሰሩ ይናገራሉ፡፡  አሁንም በሰራተኛ ልሸፍት ኃላፊነት እዚያው እሳት አደጋ ውስጥ በመስራት ላይ ናቸው፡፡

 

Science & Technology
Image የምግብና የነዳጅ ፍላጎት መጨመር...

የምግብና የነዳጅ ፍላጎት መጨመር ደንን እያወደመ ነው

የምግብና የነዳጅ ሰብሎችን ማምረት እንዲሁም የእንጨት ፍላጎት መጨመር የደን መጥፋትን ያስከትላል ሲል የ"ዘ ራይትስ ኤንድ ሪሶርስስ ኢንሽየቲቭ" ሪፖርት አስጠንቅቋል፡፡

 

 
Diaspora
Image በትውልድ አገራቸው በልማት...
በትውልድ አገራቸው በልማት ውጤታማ የሆኑትን ማስተዋወቅ ይጀመራል

በምሕረት ሞገስ

ነዋሪነታቸው በኔዘርላንድስ ሆኖ በትውልድ አገራቸው አዋጭና እድገትን መሰረት ያደረገ ሥራ የሚሰሩ ዲያስፖራዎችን የማስተዋወቅ ሥራ ሊጀምሩ መሆናቸውን ሚ/ር ኢዋን ሶንደር ተቀማጭነቱን በኔዘርላንድስ ያደረገው ኢንተርናሽናል ኢንተርፕሩነርሽፕ (ኢንትኤንት) አማካሪ ገልፀዋል፡፡  

Youth
Image የወጣቶቹ ፍሬ

በጋዜጣው ሪፖርተር

የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን እንዲመጡ ማበረታቻዎች መኖር አለባቸው፡፡ አገሪቱ የፈጠራ ሥራን ካበረታታችና ከደገፈች አገሪቱን የሚጠቅሙ በርካታ የፈጠራ ባለሙያዎች ይመጣሉ፡፡ ለፈጠራ ባለቤትነት ወይም እውቅና የማይሰጥባቸው ዘርፎችም ብልሃት ሊፈለግላቸው ይገባል፡፡ በኮምፕዩተር ዘርፍ እውቅና የሚሰጠው ማን ነው? ሣይንስና ቴክኖሎጂ አቅምና ብቃቱ የለውም ወይ ለሚሉት ጥያቄዎች ምላሽ ያስፈልጋቸዋል፡፡ በፈጠራ ባለሙያዎች ዘንድ ሌላው የሚነሳው ለፈጠራ ባለቤትነት ክፍያ መፈፀሙ ተገቢ አለመሆኑን ነው፡፡ ይህንን ክፍያ መክፈል ባለመቻል ፈጣሪዎችና ፈጠራቸው ተዳፍነው ይቀራሉ የሚል ቅሬታ አለ፡፡

 

 
Opinion
ገልጦ የሚያይ 'አምላክ'ማ አይከለክልም

በሪሁን ተሻለ

የአገራችንን የሥራ ፈላጊዎች፣ ሥራ አጦችን፣ ሥራ ፈላጊዎችን፣ ሥራ ላይ ሆነው፣ ሥራ እያላቸው የተሻለ ሥራ የሚያፈላልጉትን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በላይ በሚገኝ ከፍተኛ ሥራ የፖለቲካ ሥልጣን ላይ ያሉትን ጭምር ሲበዛ ሊያሰገርም ሊያስደንቅ የሚችል አንድ "የሥራ ማስታወቂያ" ያየሁት በአሜሪካው የዋይት ሀውስ ዌብ ሳይት (ድረ ገጽ) ላይ ነው፡፡ ከ115 ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የሚደረገው የአሜሪካ የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ከስልጣን የሚሰናበተውና የሚተካውን ግለሰብ/ ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን ፓርቲውንም ጭምር አብሮን ከእኛ ጋር የሚያውቀው የቡህ ቸኒ አስተዳደር ይህንን የሥራ ማስታወቂያ ወይም የከፍተኛ ሹመት ማመልከቻ ጥሪ በዋይት ሀውስ ድረ ገጽ ላይ የለጠፈው ሥልጣን ከያዘበት ከስምንት ዓመት ወዲህ ጀምሮ ነው፡፡ ዛሬም አሁንም አለ፡፡

 

Letter to Reporter
ዱላ ቀረሽ አስተያየት
የሀገር መሪ የቃላት አጠቃቀሙ፣ የፊቱ ሁኔታና የድምፅ አወጣጡ ሁሉ ትርጉም እንደሚኖረው በሐምሌ 6/2000 ሪፖርተር ጋዜጣ በእኔ የምለው ጉድ ተጠቅሷል፡፡ የሚያስቆጣና የሚያበሳጭ ጉዳይ ቢያጋጥመው እንኳ በተረጋጋ መንፈስ የመናገር ብቃት ሊኖረው ይገባል፡፡ አለበለዚያ ንዴትና ብስጭት በተቀላቀለበት መልክ በቁጣ ለመመለስ መሞከር እርምጃ ለመውሰድ የተዘጋጀ ያስመሰልዋል፡፡ ማስፈራራትም ይመስላል፡፡ እነዚህ ሁሉ ተደማምረው መተማመንን ያመነምናሉ፡፡ ባለሙያዎቹም እየራቁ ይሄዳሉ፡፡

 
Women
Image ፣የዓመቱ ምርጥ የፈጠራ ሴት፣

በምህረት አስቻለው

"መንገድ ላይም ይሁን በማንኛውም ቦታ የሰዎችን አለባበስ በትኩረት እመለከታለሁ፡፡ እዚህ ጋር እንዲህ፣ ቀለሙ የዚህ ዓይነት ቢሆን ብዬ አስባለሁ፡፡ የማውቀው ሰው ከሆነ ደግሞ አስተያየት እሰጣለሁ፡፡ ማንኛውም ሰው በሄደበት ሁሉ ከሙያው ጋር የሚገናኙ ነገሮችን ማስተዋሉ አይቀርም፡፡ የምገዛቸው ልብሶችንም ቢሆን በምፈልገው መንገድ አስተካክላቸዋለሁ" ትላለች ፣የዓመቱ ምርጥ የፈጠራ ሴት፣ ተብላ ሽልማት ማግኘት የቻለችው የልብስ ዲዛይነር፡፡

 

Temuaget
ዋናው ተቆጣጣሪ!
ከጎይቶም አዳነ

ዋናው ኦዲተር የሁሉም፣ የሦስቱም የኢትዮጵያ ሕገመንግስቶች ጉዳይ ሆኖ ኖሯል፡፡ በሌላ አነጋገር ዋናው ኦዲተር ሕገመንግስታዊ የሥልጣን አካል ስለመሆኑ በተለይም በሦስቱ ሕገመንግስቶች የተፈፃሚነት ዘመን ውስጥ እውነት ነበር፡፡

 
Law
Image ለኦዲዮ ቪዥዋል ሥራ ኘሮዲውሰሩ ማን ነው?
በሰለሞን ጐሹ

ሰኔ 22 ቀን 2ዐዐዐ ዓ.ም. በወጣው የሪፖርተር ጋዜጣ ‘ኪንና ባህል’ ዓምድ ላይ (“ለአባቷ” ፊልም ብሩክ ፊልሞችንና ናቭኮም ኢነርጂን እያወዛገበ ነው) በሚል ርዕስ ማስነበባችን ይታወሳል፡፡ በወቅቱ የናቭኮም ኢነርጂ ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር አድማሱ ገብሬ ምላሽ ለመስጠት ባይችሉም ከፅሁፉ መውጣት በኋላ ብሩክ ፊልሞች አሳስቷል ባሏቸው ነጥቦች ላይ ከአሉላ ኤ.አንደሚካኤል ጋር በመሆን ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

Zennk
የፍቅር አይነቶች

ግሪኮች ለፍቅር ሦስት ዓይነት ስያሜ ሲሰጡት ሮማውያንም እንዲሁ በሦስት ይከፍሉታል፡፡ በግሪክ የመጀመሪያው ዓይነት ፍቅር "ኤሮስ" የሚሉት ሲሆን ይኸውም ከፍትወት ፍቅር ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው፡፡ ሁለተኛው ዓይነት ፍቅር ደግሞ "ፊሎ" ይሉታል፡፡ ይኸ ደግሞ እንደ ፊሎዞፊ የራሱ የሆነ ሥነ ቃል ሲሆን ይኸውም የሰው ልጅ ፍቅር ወይም የጥበብ ፍቅር ተደርጐ ይወሰዳል፡፡ ሦስተኛው ዓይነት ፍቅር "አጋፔ" የሚሉት ነው፡፡ ይኸ ዓይነቱ ፍቅር ለአምላክ የሚኖርን ፍቅር በቀጥታ የሚመለከት ነው፡፡

 

 
Delalaw
ቁዘማ
እኛ ለማዘንም ሆነ ለመደሰት ጊዜ አይፈጅብንም፡፡ ወደ  ይሁን ወደቀኝ  ቢሉ ደስታና ሐዘን፣ ረሃብና ጥጋብ ጎን ለጎን ያገኟቸዋል፡፡ ድሎትና ብሶት፣ ጥፋትና ልማት ጎን ለጎን፡፡ ሳይራራቁ፣ ሳይለያዩ ቅርብ ለቅርብ ናቸው፡፡ ለዚህ ዋቢ መጥራት አያስፈልግም፡፡

Teles
በግልፅነት የተገኘ ለውጥ

በጋዜጣው ሪፖርተር

ሸመቱና ጓደኛዋ ስራነሽ ለማንም የማይነግሩትና ለሁለት ዓመታት በጋራ የያዙት ሚስጢር አላቸው፡፡ ኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በደማቸው መኖሩንና የፀረ ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት መውሰድ ከጀመሩ ሁለት ዓመታት ማሳለፋቸውን ለማንም ለመንገር አይደፍሩም፡፡

 

 
Sport
Image "ከፖሊሲው በተቃራኒ ፌዴሬሽኖችን...

"ከፖሊሲው በተቃራኒ ፌዴሬሽኖችን ወደ አንድ ዕዝ ለመመለስ ይመስላል"
አቶ ተስፋዬ ሽፈራው የኢትዮጵያ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት


የኢትዮጵያ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ከአትሌቲክስና ቦክስ ፌዴሬሽኖች ቀጥሎ በኢንተርናሽናል የውድድር መድረክ ኢትዮጵያን የሜዳሊያ ባለቤት አድርጓል፡፡ ይሁንና ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ በአሁኑ ሰዓት በምንም መመዘኛ እውቅና ለሌለው ማርሻል አርት ለሚባል ፌዴሬሽን ሙሉ ጽ/ቤቱ እንደተሰጠበትና ያለ ቢሮ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የኢትዮጵያ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ተስፋዬ ሽፈራው ይገልፃሉ፡፡ አነጋግረናቸዋል፡፡

 

Taxi
ተሞክሯችን
ኑሮ የጎነተላቸው ተሳፋሪዎች ከጀርባዬ ሆነው ሲያወሩ ይሰማኛል፡፡ የገቢ ምንጭን ማብዛት ባለመቻላቸው ተቸግረዋል፡፡ ለዚህ ችግራቸው አማራጭ ያደረጉት በየዕለቱ ፍላጎታቸውን መቀነስ ነው፡፡ ሻይ ቡና፣ መክሰስ ብሎ ነገር እየቀረ ነው፡፡ ቁርስም ቢሆን ማስመሰል እንጂ መብላት አይደለም፡፡ የኑሮ ውድነቱ በፍጥነት እየቀጠለ ሲሄድ የዳቦው መጠንም በዚያው ፍጥነት ያፈገፍጋል፡፡ እያነሰ፣ እያነሰ ነጥብ ለሆን ነው፡፡ የአንዳንዶቻችን ቁርስ በየቀኑ እያነሰ፣ እያነሰ የሚሄደውን ዳቦ በሻይ ማለት ነው፡፡ ይህም ቢሆን መካከለኛ ገቢ ባላቸው ዘንድ ነው፡፡

 
World
እስራኤል በኢራን ላይ እርምጃ...

እስራኤል በኢራን ላይ እርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀቷን ገለፀለች
በጋዜጣው ሪፖርተር

እስራኤል ጥቃት ይደርስብኛል የሚል ስጋት ካደረባት በኢራን ላይ እርምጃ ለመውሰድ የተዘጋጀች መሆኗን መከላከያ ሚኒስትሩ ገለፁ፡፡

 

 
  • Do You Know ?
    How To Increase Font Size
    You can increase the font size of the website if it appears smaller than normal. Just click the member area link at the top right of this page and the page will slide down. At the top left corner of the page, look for three small buttons. To increase font size, click the button with "+" sign and "-" sign to decrease font size.
  • Tips !
    Tips for Amharic Version
    • Use Internet Explorer version 6 or better
    • Adjust your screen resolution to 1024 X 768
    • Use the font resizer to increase font size if needed
    • Though it is not strictly needed having power geez unicode font could enhance the font rendering in your browser
 

Important Links

Visit Ethiopian Yellow PagesA forum on Dialogue, Democracy & Development