| ያልተገባ ድርጊት |
|
| Wednesday, 09 January 2008 | |
|
ታህሳስ 20 ቀን 2000 ዓ.ም በ..እኔ የምለው.. ገጽ በፓትርያሪኩ ..ያልተገባ ድርጊት.. ዙሪያ የቀረበውን ጽሁፍ አንብቤ እኔም የራሴን ማለት እንዳለብኝ ወሰንኩ፡፡
ፓትሪያሪካችን በየጊዜው በእንዲህ ዓይነት ያልተገባ ድርጊት ላይ መሰማራታቸው የራሳቸው ጊዜያዊና ዘለቄታዊ ባህሪይ ብቻ አይመስለኝም፡፡ አጠገባቸው ያሉ አማካሪዎቻቸውና የቤተክህነት ሰዎች እንዲሁም እኛ (ማኅበረ ምዕመናን) እጃችን አለበት፡፡ አጠገባቸው ያሉ አማካሪዎቻቸውና የቤተክህነት ሰዎች ተጠያቂ ናቸው፡፡ በፓትርያሪኩ አጠገብና ዙሪያ ያሉ ሰዎች በእርሳቸው መንፈሳዊ አባትነት እየተመራ ያለው ማኅበረ ምዕመናን ምን አይነት መንፈሳዊ ግልጋሎት እየተሰጠው እንዳለና በመንፈሳዊ አባትነታቸው ሊፈቱለት የሚገቡ ችግሮችንና አጠቃላይ ሁኔታዎችን እንዳያዩ አድርጓቸዋል፡፡ ለዚህም አብነት የሚሆኑን ጽሁፎችን ይዞ በሚወጣው የቤተክርስቲያኗ ልሳን የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪዎችና የቅኔ ባለሙያዎች የሚቀርብላቸው ውዳሴና ቅኔ (ሙገሳና ውዳሴ ከንቱ የበዛበት) ማንበብና መመልከት ይበቃል፡፡ በእነዚህ መልካምነታቸውና የተጋነነ ሙገሳ ብቻ የሚቀርብላቸውን የሚሰሙትና የሚያነቡት ቅዱስ ፓትሪያሪካችን ፎቶአቸውን በትላልቅ አድባራት እያስለጠፉ ..ሕዝቡ ስለሚወደኝ ነው፡፡ ምንም ችግር የለም፡፡ ይገባኛል.. ነው የሚሉት፡፡ ለፓትርያሪካችን የማሳስበው እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥታ ከሕዝቡ (ከምዕመናኑ) ጋር የሚገናኙበትን መንገድ ይፈልጉና ትክክለኛውን የሕዝብ አመለካከት ይረዱ፡፡ ለችግሮች ትክክለኛውን መፍትሄ ይስጡ፡፡ ዳግመኛ እንዲህ አይነት ክፍተት በመሪና በተመሪ መሃል እንዳይፈጠርም የተሻለ አስተዳደራዊ መዋቅር ይበጅ፡፡ (ኃይለ ገብርኤል፣ ከአማኑኤል) |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |