Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Friday
Jul 04th
Home arrow Sections arrow ኦፌዴን ከምርጫው ራሱን አገለለ
ኦፌዴን ከምርጫው ራሱን አገለለ Print E-mail
Wednesday, 16 April 2008
Image
አቶ ቡልቻ ደመቅሳ
ዛሬ ይፋ መግለጫ ይሠጣል


የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዴን) በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ደረሰብኝ ካለው ወከባ ጋር በተያያዘ በመጪው እሁድ ከሚካሄደው ምርጫ ራሱን ማግለሉን ምንጮች አረጋገጡ፡፡ ፓርቲው በጉዳዩ ላይ በዛሬው እለት በይፋ መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል፡፡

ኦፌዴን አባሎቼን፣ ደጋፊዎቼን እና ገና ለገና ፓርቲው በእጩነት ያቀርባቸዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎችን የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች፣ የቀበሌና የወረዳ ሹማምንት በማዋከብ፣ በማሳደድ፣ በማሰር፣ የሐሰት ክስ በመመስረት የተጠናከረ ዘመቻ አካሂደውብኛል የሚል ስሞታ በተደጋጋሚ አቅርቧል፡፡ ፓርቲው ደርሶብኛል ያላቸውን ችግሮች ለምርጫ ቦርድ አቅርቦ ቦርዱ ምንም ዓይነት መፍትሄ ሊሰጠው እንዳልቻለም አስታውቋል፡፡

አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስለጉዳዩ ማብራሪያ ተጠይቀው አቋማችንን በዛሬው እለት በምንሰጠው መግለጫ እናስታውቃለን በሚል አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡

ባለፈው እሁድ እትማችን ኦፌዴን በገዢው ፓርቲ ወከባ፣ እሥራት፣ እንግልት እንደደረሰበት፣ ሆኖም ፓርቲው ከምርጫው ራሱን ማግለሉን ቢገልፅ በተለይ በገጠር አካባቢ ከፓርላማ ጭምር ራሱን ያገለለ ያስመስላል በሚል ላለመውጣት እንደወሰኑ አቶ ቡልቻን ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በምርጫ ቦርድ ኘሮግራም መሠረት በአዲስ አበባ ባለፈው እሁድ የፓርላማ የማሟያ እና የከተማ አስተዳደር ምርጫ የተካሄደ ሲሆን በመጪው እሁድ ደግሞ የክፍለ ከተማና የቀበሌ አስተዳደሮች ምርጫ እንደሚካሄድ መገለፁ ይታወሳል፡፡

ባለፈው ሳምንት በኘሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የሚመራው ኢዴኀህ ተመሳሳይ እርምጃ መውሰዱ አይዘነጋም፡፡

በጋዜጣው ሪፖርተር
 
< Prev   Next >