| ኦፌዴን ከምርጫው ራሱን አገለለ |
|
|
| Wednesday, 16 April 2008 | |
![]() አቶ ቡልቻ ደመቅሳ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዴን) በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ደረሰብኝ ካለው ወከባ ጋር በተያያዘ በመጪው እሁድ ከሚካሄደው ምርጫ ራሱን ማግለሉን ምንጮች አረጋገጡ፡፡ ፓርቲው በጉዳዩ ላይ በዛሬው እለት በይፋ መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል፡፡ ኦፌዴን አባሎቼን፣ ደጋፊዎቼን እና ገና ለገና ፓርቲው በእጩነት ያቀርባቸዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎችን የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች፣ የቀበሌና የወረዳ ሹማምንት በማዋከብ፣ በማሳደድ፣ በማሰር፣ የሐሰት ክስ በመመስረት የተጠናከረ ዘመቻ አካሂደውብኛል የሚል ስሞታ በተደጋጋሚ አቅርቧል፡፡ ፓርቲው ደርሶብኛል ያላቸውን ችግሮች ለምርጫ ቦርድ አቅርቦ ቦርዱ ምንም ዓይነት መፍትሄ ሊሰጠው እንዳልቻለም አስታውቋል፡፡ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስለጉዳዩ ማብራሪያ ተጠይቀው አቋማችንን በዛሬው እለት በምንሰጠው መግለጫ እናስታውቃለን በሚል አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ ባለፈው እሁድ እትማችን ኦፌዴን በገዢው ፓርቲ ወከባ፣ እሥራት፣ እንግልት እንደደረሰበት፣ ሆኖም ፓርቲው ከምርጫው ራሱን ማግለሉን ቢገልፅ በተለይ በገጠር አካባቢ ከፓርላማ ጭምር ራሱን ያገለለ ያስመስላል በሚል ላለመውጣት እንደወሰኑ አቶ ቡልቻን ጠቅሰን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ በምርጫ ቦርድ ኘሮግራም መሠረት በአዲስ አበባ ባለፈው እሁድ የፓርላማ የማሟያ እና የከተማ አስተዳደር ምርጫ የተካሄደ ሲሆን በመጪው እሁድ ደግሞ የክፍለ ከተማና የቀበሌ አስተዳደሮች ምርጫ እንደሚካሄድ መገለፁ ይታወሳል፡፡ ባለፈው ሳምንት በኘሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ የሚመራው ኢዴኀህ ተመሳሳይ እርምጃ መውሰዱ አይዘነጋም፡፡ በጋዜጣው ሪፖርተር |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |