Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 20th
Home arrow Sections arrow የውኃ ሃብት የሥራ ፈቃድና...
የውኃ ሃብት የሥራ ፈቃድና... Print E-mail
Sunday, 20 April 2008
የውኃ ሃብት
የሥራ ፈቃድና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰጠ


የውኃ ሃብት ሚኒስቴር በውሃ ነክ ሥራዎች ላይ ለተሰማሩ ከ800 በላይ ለሚሆኑ ድርጅቶች እና ባለሙያዎች ባለፉት ዘጠኝ ወራት የሥራ ፈቃድና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት መስጠቱን አስታወቀ፡፡

 

ከእነዚህም መካከል የሥራ ፈቃድ የተሰጣቸው 675 ባለሙያዎች፣ 96 ኮንትራክተሮችና 15 አማካሪ ድርጅቶች ሲሆኑ ሌሎች 12 ድርጅቶች እና 54 ባለሙያዎች ደግሞ የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮና ጠረጋ ሥራ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርቲፊኬት ማግኘታቸውን አስረድቷል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የ15 አነስተኛ ከተሞች የውኃ ተቋማት ጥናትና ዲዛይን፣ እንዲሁም የ30 ከተሞች ዲዛይን፣ የስምንት ከተሞች ውኃ ተቋማት ማስፋፊያና ማሻሻያ ጥናትና የ60 ከተሞች አዳዲስ የውኃ ተቋማት ግንባታ ማስፋፊያ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጿል፡፡

ከ15 ሺህ ሕዝብ በታች ያላቸው የ31 ከተሞች አስቸኳይ መልሶ ማቋቋም፣ ጥገናና ማስፋፊያ ሥራዎች ለማጠናቀቅና ሌሎች የ56 ከተሞች የፊዚቢሊቲ ጥናትና የቢዝነስ ፕላን ዝግጅት፣ እንዲሁም የዲዛይን ሥራዎች ለማካሄድ ታቅዶ የ31 ከተሞች የአስቸኳይ መልሶ ማቋቋም ጥገናና የማስፋፊያ ሥራዎች መጠናቀቃቸውን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ አመልክቷል፡፡

በተጠናቀቁ የውኃ ተቋማት በአጠቃላይ 105 ሺህ 600 ነዋሪዎች ተጠቃሚ መሆናቸውን፣ 1 ሺህ 538 የገጠር የውኃ ተቋማትን ለመገንባት ታቅዶ የ1 ሺህ 400 ተቋማት ግንባታ ሥራ መከናወኑንና በዚህም 454 ሺህ 639 ነዋሪዎች የንጹህ መጠጥ ውኃ ማግኘታቸውን ሚኒስቴሩ አስረድቷል፡፡

 
< Prev   Next >