| ቢዮንሴ ረታች |
|
| Wednesday, 09 January 2008 | |
|
ቤቢ ቦይ የተሰኘው ዘፈኗን ጄኒፈር አርሙር ከእኔ የተወሰደ ሥራ ነው በማለቷ ቀርቦባት የነበረውን የኮፒ ራይት ክስ ቢዮንሴ መርታቷን የቢቢሲ ዘገባ አመልክቷል፡፡
ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ የክስ ክርክሩ የቆየ ሲሆን፣ ቢዮንሴ ..በሥራው ላይ ለተሳተፉት ሁሉ ውሳኔው ተስፋ ሰጭ ነው.. ብላለች፡፡ አርሙር ..አይ ጐት ኤ ሊትል ቢት ኦፍ ላቭ ፎር ዩ.. የሚለውን ዘፈን ለቢዮንሴ ማናጀር በ1995 ዓ.ም ሪከርድ እንዲያደርግላት ሰጥታው እንደነበረ፣ በዚያ ወቅትም ኮፒ እንደተደረገባት የተናገረች ቢሆንም በሂዩስተን የዋለው የቴክሳስ ችሎት የቢዮንሴ ..ቤቢ ቦይ.. ከዚያ በፊት የተሠራ ነው በማለት ውድቅ አድርጐባታል፡፡
የአና ፍራንክ ዲያሪ በሙዚቃ ሊቀርብ ነው በናዚ የማጎሪያ (የኮንሰንትሬሽን) ካምፕ በ1945 አካባቢ የሞተችው አና ያሰፈረችው ዲያሪ (የዕለት ውሎ ማስታወሻ) በስፓኒሽ ሙዚቃ ሊቀርብ ነው፡፡ የትርዒቱ ዳይሬክተር ራፋኤል አልቬሮ በመድረኩ ዝግጅት ወቅት ከስሜታዊነት የዘለለ የትራጂክ ኦፔራ እንደሚቀርብ ተናግሯል፡፡ የአና ዲያሪ በእሷና በቤተሰቦቿ ውስጥ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ ናዚ በአምስተርዳም ያደረሰውን ሰቆቃ የሚገልፅ ሲሆን፣ በዓለም ላይ በሚሊዮኖች እንደተነበበ ይታወሳል፡፡ ..የአና ማስታወሻ.. በሚል በአማርኛ መተርጐሙም ይታወቃል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |