| ታታ የመኪና መገጣጠሚያ... |
|
|
| Saturday, 26 April 2008 | |
|
ታታ የመኪና መገጣጠሚያ ለመገንባት እየተዘጋጀ ነው
የሕንድ የመኪና አምራች የሆነው ታታ ኩባንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በሰባት አገራት ውስጥ የተለያዩ ሞዴል ያላቸው ተሽከርካሪዎች የመገጣጠሚያ ፋብሪካዎችን ለመገንባት በመዘጋጀት ላይ መሆኑን አስታወቀ፡፡ የኩባንያው የአፍሪካ ተወካይ ለኢንዲያን ታይምስ እንዳስታወቁት፣ በአሁኑ ጊዜ ትልቅ ኢንቨስትመንት ያላቸው በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ነው፡፡ እስካሁን ባለው የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴያቸውም በደቡብ አፍሪካና በሌሎች የደቡባዊ አፍሪካ አገሮች ከ1.4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስት አድርገዋል፡፡ እስከ እ.ኤ.አ 2010 ባለው ጊዜ ውስጥ ደግሞ ኢትዮጵያን ጨምሮ 7 በሚሆኑ አገራት ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ወጪ በማድረግ የተሽከርካሪዎች መገጣጠሚያና ከዚሁ ሥራ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ኢንቨስትመንቶችን ውስጥ እንደሚገቡ ለዚህም የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶች በማድረግ ላይ መሆናቸውን ተወካዩ አመልክተዋል፡፡ ታታ በአፍሪካ ውስጥ ያለውን የኢንቨስትመንት ፍሰቱን በእቅዱ መሰረት የሚተገብር ከሆነ በአፍሪካ ውስጥ ያለው ኢንቨስትመንት ከ2.5 ቢሊዮን ብር በላይ እንዲደርስ ያደርገዋል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |