Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 20th
Home arrow Sections arrow ከ600 በላይ ተፈናቃዮች...
ከ600 በላይ ተፈናቃዮች... Print E-mail
Saturday, 26 April 2008
ከ600 በላይ ተፈናቃዮች ለችግር ተጋለጡ

ከኤርትራ ተፈናቅለው በአድዋ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ከ600 በላይ የሚሆኑ ተፈናቃዮች የመቋቋሚያ ገንዘብ ስላልተሰጣቸው ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን ምንጮች አስታወቁ፡፡ የትግራይ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ቢሮ የእርዳታ ፕሮግራም ኃላፊ ደግሞ የመቋቋሚያው ገንዘብ እንደደረሰ ወዲያውኑ እንደሚታደላቸው ገልፀዋል፡፡

 

ምንጮች እንዳመለከቱት እስካሁን ባለው አሠራርና ደንብ ተፈናቃዮቹ መጠለያ ጣቢያ ከገቡ ከአንድ ሳምንት በኋላ ለመቋቋሚያ የሚሆን በነፍስ ወከፍ 3ሺህ ብር እየተሰጣቸው ወደየዘመዶቻቸው እንዲቀላቀሉ ይደረግ ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን ያሉት ተፈናቃዮች መጠለያ ከገቡ ሁለት ወር እንደሞላቸው፣ ቁርስ ምሳና ራት ከሚቀርብላቸው በስተቀር እስካሁን መቋቋሚያ እንዳልተሰጣቸው አስረድተዋል፡፡

ኃላፊው አቶ ፍስሀ ታወቀ በበኩላቸው የመቋቋሚያ ገንዘብ እንዲላክ ለፌዴራል አደጋ መከላከልና ዝግጁነት ኤጀንሲ ጥያቄ መቅረቡን፣ በጥያቄው መሰረት ገንዘቡ እንደተላከ ወዲያውኑ የማከፋፈሉ ሥራ እንደሚቀጥል አስረድተዋል፡፡

የፌዴራል አመዝኤ የእርዳታ ፕሮግራም አፈፃፀምና ክትትል መምሪያ ኃላፊ ስለዚሁ ጉዳይ እንዲያነጋግሩን በፀሐፊያቸው አማካይነት በስልክ ጠይቀናቸው ወደ ሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት መርተውናል፡፡

አቶ ሲሳይ ታደሰ የፌዴራሉ አመዝኤ የሕዝብ ግንኙነት ቡድን መሪ በበኩላቸው ቀደም ሲል ለመቋቋሚያ የሚሆን ገንዘብ ከማዕከሉ ይላክ እንደነበር አሁን ግን ይህ አይነቱ አካሄድ ቀርቶ ክልሎች ራሳቸው እንዲሸፍኑ መደረጉን አስረድተዋል፡፡

 
< Prev   Next >