| በሐረር ከተማ የመሬት የሊዝ እዳ... |
|
|
| Wednesday, 30 April 2008 | |
|
በሐረር ከተማ የመሬት የሊዝ እዳ አከፋፈል ውዝግብ አስነሳ
በተሾመ ንቁ በሐረር ከተማ የተሰማሩ ኢንቨስተሮች ከአስር አመት በላይ የተጠራቀመ የመሬት የሊዝ እዳ ክፍያ እንድንከፈል ተጠይቀናል ሲሉ አማረሩ፡፡ የከተማው መስተዳድር የክፍያው ሁኔታ ፍትሐዊ መሆኑን በመግለፅ አቤቱታውን አስተባበለ፡፡ በሐረር ከተማ በኢንቨስትመንት መስክ የተሰማሩ ባለሀብቶች፤ ከ1986 ዓ.ም. ጀምሮ ታሳቢ የሚደረግ የሊዝ እዳ ክፍያ መጠየቃቸውን በመግለፅ፤ የእዳ እሳቤውን ተቃወሙ፡፡ ባለሀብቶቹ አንደኛ ደረጃ በካሬ ሜትር 650 ብር ሁለተኛ ደረጃ 550 ብር፣ ሦስተኛ ደረጃ 5ዐዐ ብር ታሳቢ የሚደረግ ክፍያ መጠየቃቸውን አስታውቀዋል፡፡ በዚህም የመሬት ርክክብ ሲደረግ የክፍያ መጠኑ ያልተወሰነ መሆኑን በመጥቀስ ፍትሐዊ ያልሆነ ከፍተኛ ክፍያ መጠየቃቸውን ገልፀዋል፡፡ ባለሀብቶቹ ከከተማው አስተዳደር ጋር የኢንቨስትመንት ውል ሲገቡ የክፍያ መጠን ካሬ ሜትር ተተምኖ ያልተገለፀላቸው መሆኑን በመጥቀስ፤ አስተዳደሩ ያስታወቃቸው የሊዝ ክፍያ መጠን ድንገተኛ እንደሆነባቸው ገልፀዋል፡፡ በዚህም "የከተማው አስተዳደር ከውል ውጪ ከፍተኛ ክፍያ ጠይቆናል" ሲሉ አማርረዋል፡፡ ባለሀብቶቹ የከተማው አስተዳደር የክፍያ ሁኔታውን ለረዥም ጊዜ ሳያሳውቃቸው ቆይቶ፤ በያዝነው ወር ድንገተኛ የክፍያ ውዝፍ መግለፁን ተቃውመዋል፡፡ በተሰጣቸው መሬት ላይ ግንባታ ማከናወናቸውን በመጥቀስ፤ በቅርቡ የተገለፀላቸውን የሊዝ እዳ ለማስከፈል አስተዳደሩ በመሬቱ ላይ የገነቡትን ግንባታ በመያዣነት እንደያዘባቸው ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም የከተማው አስተዳደር ከአስር ዓመት በላይ የተጠራቀመውን እዳ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲከፍሉ ማስገደዱን ጠቅሰዋል፡፡ እንደ ባለሀብቶቹ ገለፅ አንድ ባለሀብት በሊዙ እሳቤው ከአንድ እስከ አራት ሚሊዮን ብር ለመክፈል የሚገደድ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ባለሀብቶቹ የሊዝ ክፍያውን በመቃወም የፊርማ ማሰባሰብ ሥራ መጀመራቸውን ገልፀዋል፡፡ የተቃውሞ ፊርማውንም ለሚመለከታቸው የከተማው፣ የክልሉና የፌደራል መንግሥት አመራሮች እንደሚያስታውቁ ገልፀዋል፡፡ የሐረር ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ አሪፍ መሀመድ በበኩላቸው የክልሉ ምክር ቤት እስከ 1999 ዓ.ም. ድረስ የሊዝ ደንብ ያልነበረው መሆኑን ጠቅሰው፤ "የሊዝ ደንቡ ትግበራ መዘግየቱ የክልሉ አስተዳደር ችግር ነበር" ሲሉ ገልፀዋል፡፡ አቶ አሪፍ የሊዝ ደንቡ ዘግይቶ ቢፀድቅም ኢንቨስተሮች እዳቸውን መክፈል እንደሚገባቸው ገልፀዋል፡፡ የክፍያው ሁኔታ በተለያየ የከተማው የይዞታ ደረጃ በካሬ ሜትር ከ150 እስከ 650 ብር መሆኑን የገለፁት አቶ አሪፍ፣ ባለሀብቶች የሊዝ አዋጅ በፌዴራል ደረጃ ከወጣበት ከ1986 ዓ.ም. ጀምሮ ያለባቸውን እዳ መክፈል እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡ የአከፋፈሉ ሁኔታ ግን በአንድ ጊዜ አለመሆኑን ሥራ አስኪያጁ ገልፀው፤ የክፍያ ጊዜውን በተመለከተ መመሪያ የማውጣት ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ አቶ አሪፍ በከተማው በኢንቨስትመንት የተሰማሩ ባለሀብቶች መሬት ሲረከቡ በሊዝ ደንብ ክፍያ ለመፈፀም በገቡት ውል መሠረት ክፍያ እንዲፈፅሙ መደረጉ አግባብ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ "ባለሀብቶቹ አሁን የተጠየቁት ውዝፍ እዳ እንዲከፍሉ ሳይሆን፤ የ2ዐ በመቶ የቅድሚያ ክፍያ ነው" ሲሉ አስተባብለዋል፡፡ የከተማው ባለሀብቶች በሊዝ ህጉ መሠረት የሊዝ ውለታቸውን እንዲፈርሙ፣ አዲሱን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲወስዱ ስራ አስኪያጁ አሳስበዋል፡፡ ሥራ አስኪያጁ የከተማው አስተዳደር ባለሀብቶቹ የሀያ በመቶው የቅድሚያ ክፍያ ውጭ ያለውን የውዝፍ ሂሳብ አከፋፈል በተመለከተ ፍትሀዊ የክፍያ ጊዜ እያመቻቸ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በዚህም የክፍያ ጊዜው እስከ ሀያ አመት ሊደርስ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡ በቅድሚያ ክፍያ አከፋፈል መሠረት ሁለት መቶ ካሬ ሜትር የያዘ ባለሀብት ከአርባ እስከ ሀምሳ ሺህ ብር ብቻ የሚከፍል መሆኑን ጠቅሰው፤ "ክፍያው የባለሀብቱን የኢንቨስትመንት ሥራ የሚያደናቅፍ አይደለም" ብለዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር በሆቴል፣ በቱሪዝምና በህክምና የተሰማሩ ኢንቨስተሮች ከ50 እስከ 60 በመቶ ቅናሽ እንደሚደረግላቸው አቶ አሪፍ ገልፀዋል፡፡ ስራ አስኪያጁ በከተማው ከተሰማሩት ኢንቨስትሮች አብዛኛው ከ1995 ዓ.ም. ወዲህ ውል የገቡ በመሆናቸው ከፍተኛ ውዝፍ እዳ በባለሀብቱ ላይ እንደማይኖር ገልፀዋል፡፡ ከባለሀብቶች ጋር ውይይት መጀመራቸውንና ከሀያ በላይ ኢንቨስተሮች ክፍያ መጀመራቸውን አቶ አሪፍ ገልፀዋል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
ኢንቨስተሮችን ለመሳብ እንረባረብ!
በእንስሳት ማድለብ ሥራ 1ዐ ሚሊዮን ብር ትርፍ ተገኘ
በትግራይ ማዕከላዊ ዞን ስምንት ወረዳዎች በእንስሳት ማድለብ ሥራ የተሰማሩ አርሶ አደሮች አስር ሚሊዮን ብር ትርፍ ማግኘታቸውን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ፡፡
የሆላንድ ካርን ድርሻ ለመግዛት...
"ካለን ውስን የሰው ኃይል፣ ፋይናንስና...
(ሚኒስትር መሥሪያ ቤት በኃላፊነት እንዲያሳካ የተሰጠውን ፕሮጀክት የሚገመግም ከአገር ውስጥና ከውጭ የተውጣጣ የኤክስፐርቶች ቡድን ክቡር ሚኒስትሩ መሥሪያ ቤት ድረስ መጥቷል፡፡ እሳቸውም ከባለሙያዎቻቸው ጋር ናቸው፤ ስብሰባው ተጀምሯል)
ጀግኖቻችንን ለማክበር
በሔኖክ ያሬድ
በኢትዮጵያ ከስም የዋለ ተግባር ያከናወኑ ምርጥ ሰዎች መኖራቸው፣ ማለፋቸው የተመዘገበ ነው፡፡ በጀግንነትም ይጠቀሳሉ፡፡ ከሰብዓዊ ጥናት በተለይም በኪነ ጥበባት ዘርፍ አንቱ የተባሉ ኢትዮጵያውያን የመኖራቸውን ያህል በጦር ውሎ የተወደሱት ጀግኖች ያህል ክብር የተሰጣቸው ምን ያህል እንደሆኑ እምብዛም አይታወቅም፡፡
"ጃንጥላና ሹራብ ሰሪ ክረምት ይወዳል"
በምህረት አስቻለው
መርካቶ ራጉኤል ቤተክርስቲያን አቅራቢያ ከሚገኝ አንድ የልብስ ሱቅ ደጃፍ ላይ የተበላሹ ጃንጥላዎችን ሲጠግኑ አገኘኋቸው፡፡ አቶ አራርሳ ሔርጶ ለሃያ ዓመታት በእሳት አደጋ መከላከያ ብርጌድ ውስጥ በጥበቃነት፣ በአደጋ ተከላካይነት እንደሰሩ ይናገራሉ፡፡ አሁንም በሰራተኛ ልሸፍት ኃላፊነት እዚያው እሳት አደጋ ውስጥ በመስራት ላይ ናቸው፡፡
የምግብና የነዳጅ ፍላጎት መጨመር...
የምግብና የነዳጅ ፍላጎት መጨመር ደንን እያወደመ ነው
የምግብና የነዳጅ ሰብሎችን ማምረት እንዲሁም የእንጨት ፍላጎት መጨመር የደን መጥፋትን ያስከትላል ሲል የ"ዘ ራይትስ ኤንድ ሪሶርስስ ኢንሽየቲቭ" ሪፖርት አስጠንቅቋል፡፡
በትውልድ አገራቸው በልማት...
የወጣቶቹ ፍሬ
በጋዜጣው ሪፖርተር
የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶችን እንዲመጡ ማበረታቻዎች መኖር አለባቸው፡፡ አገሪቱ የፈጠራ ሥራን ካበረታታችና ከደገፈች አገሪቱን የሚጠቅሙ በርካታ የፈጠራ ባለሙያዎች ይመጣሉ፡፡ ለፈጠራ ባለቤትነት ወይም እውቅና የማይሰጥባቸው ዘርፎችም ብልሃት ሊፈለግላቸው ይገባል፡፡ በኮምፕዩተር ዘርፍ እውቅና የሚሰጠው ማን ነው? ሣይንስና ቴክኖሎጂ አቅምና ብቃቱ የለውም ወይ ለሚሉት ጥያቄዎች ምላሽ ያስፈልጋቸዋል፡፡ በፈጠራ ባለሙያዎች ዘንድ ሌላው የሚነሳው ለፈጠራ ባለቤትነት ክፍያ መፈፀሙ ተገቢ አለመሆኑን ነው፡፡ ይህንን ክፍያ መክፈል ባለመቻል ፈጣሪዎችና ፈጠራቸው ተዳፍነው ይቀራሉ የሚል ቅሬታ አለ፡፡
በሪሁን ተሻለ
የአገራችንን የሥራ ፈላጊዎች፣ ሥራ አጦችን፣ ሥራ ፈላጊዎችን፣ ሥራ ላይ ሆነው፣ ሥራ እያላቸው የተሻለ ሥራ የሚያፈላልጉትን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በላይ በሚገኝ ከፍተኛ ሥራ የፖለቲካ ሥልጣን ላይ ያሉትን ጭምር ሲበዛ ሊያሰገርም ሊያስደንቅ የሚችል አንድ "የሥራ ማስታወቂያ" ያየሁት በአሜሪካው የዋይት ሀውስ ዌብ ሳይት (ድረ ገጽ) ላይ ነው፡፡ ከ115 ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የሚደረገው የአሜሪካ የፕሬዚዳንትነት ምርጫ ከስልጣን የሚሰናበተውና የሚተካውን ግለሰብ/ ግለሰቦች ብቻ ሳይሆን ፓርቲውንም ጭምር አብሮን ከእኛ ጋር የሚያውቀው የቡህ ቸኒ አስተዳደር ይህንን የሥራ ማስታወቂያ ወይም የከፍተኛ ሹመት ማመልከቻ ጥሪ በዋይት ሀውስ ድረ ገጽ ላይ የለጠፈው ሥልጣን ከያዘበት ከስምንት ዓመት ወዲህ ጀምሮ ነው፡፡ ዛሬም አሁንም አለ፡፡
፣የዓመቱ ምርጥ የፈጠራ ሴት፣
በምህረት አስቻለው
"መንገድ ላይም ይሁን በማንኛውም ቦታ የሰዎችን አለባበስ በትኩረት እመለከታለሁ፡፡ እዚህ ጋር እንዲህ፣ ቀለሙ የዚህ ዓይነት ቢሆን ብዬ አስባለሁ፡፡ የማውቀው ሰው ከሆነ ደግሞ አስተያየት እሰጣለሁ፡፡ ማንኛውም ሰው በሄደበት ሁሉ ከሙያው ጋር የሚገናኙ ነገሮችን ማስተዋሉ አይቀርም፡፡ የምገዛቸው ልብሶችንም ቢሆን በምፈልገው መንገድ አስተካክላቸዋለሁ" ትላለች ፣የዓመቱ ምርጥ የፈጠራ ሴት፣ ተብላ ሽልማት ማግኘት የቻለችው የልብስ ዲዛይነር፡፡
ለኦዲዮ ቪዥዋል ሥራ ኘሮዲውሰሩ ማን ነው?
ግሪኮች ለፍቅር ሦስት ዓይነት ስያሜ ሲሰጡት ሮማውያንም እንዲሁ በሦስት ይከፍሉታል፡፡ በግሪክ የመጀመሪያው ዓይነት ፍቅር "ኤሮስ" የሚሉት ሲሆን ይኸውም ከፍትወት ፍቅር ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው፡፡ ሁለተኛው ዓይነት ፍቅር ደግሞ "ፊሎ" ይሉታል፡፡ ይኸ ደግሞ እንደ ፊሎዞፊ የራሱ የሆነ ሥነ ቃል ሲሆን ይኸውም የሰው ልጅ ፍቅር ወይም የጥበብ ፍቅር ተደርጐ ይወሰዳል፡፡ ሦስተኛው ዓይነት ፍቅር "አጋፔ" የሚሉት ነው፡፡ ይኸ ዓይነቱ ፍቅር ለአምላክ የሚኖርን ፍቅር በቀጥታ የሚመለከት ነው፡፡
በጋዜጣው ሪፖርተር
ሸመቱና ጓደኛዋ ስራነሽ ለማንም የማይነግሩትና ለሁለት ዓመታት በጋራ የያዙት ሚስጢር አላቸው፡፡ ኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በደማቸው መኖሩንና የፀረ ኤች.አይ.ቪ መድኃኒት መውሰድ ከጀመሩ ሁለት ዓመታት ማሳለፋቸውን ለማንም ለመንገር አይደፍሩም፡፡
"ከፖሊሲው በተቃራኒ ፌዴሬሽኖችን...
"ከፖሊሲው በተቃራኒ ፌዴሬሽኖችን ወደ አንድ ዕዝ ለመመለስ ይመስላል"
አቶ ተስፋዬ ሽፈራው የኢትዮጵያ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት
የኢትዮጵያ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ከአትሌቲክስና ቦክስ ፌዴሬሽኖች ቀጥሎ በኢንተርናሽናል የውድድር መድረክ ኢትዮጵያን የሜዳሊያ ባለቤት አድርጓል፡፡ ይሁንና ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ በአሁኑ ሰዓት በምንም መመዘኛ እውቅና ለሌለው ማርሻል አርት ለሚባል ፌዴሬሽን ሙሉ ጽ/ቤቱ እንደተሰጠበትና ያለ ቢሮ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የኢትዮጵያ ወርልድ ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ተስፋዬ ሽፈራው ይገልፃሉ፡፡ አነጋግረናቸዋል፡፡
እስራኤል በኢራን ላይ እርምጃ ለመውሰድ መዘጋጀቷን ገለፀለች
በጋዜጣው ሪፖርተር
እስራኤል ጥቃት ይደርስብኛል የሚል ስጋት ካደረባት በኢራን ላይ እርምጃ ለመውሰድ የተዘጋጀች መሆኗን መከላከያ ሚኒስትሩ ገለፁ፡፡
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |
Share your thought and ideas with others on our public forum. Just register here and participate on our new and improved forum. Note that all members of the old version forum have to register again to post on the new version forum.