ሁሉም ለአገሩ መስዋዕትነት ይክፈል!
"ሶማሊያውያንን ልንረዳቸው እንችላለን...
በአገሪቱ ባለፉት አምስት ዓመታት በ60 ሚሊዮን ዶላር የተካሄደው የመጀመሪያው ምዕራፍ የአርብቶ አደሩ ማህበረሰብ የልማት ፕሮጀክት ተጠናቀቀ፡፡
የመንግሥት የፋይናንስ ተቋማት...
በናታን ዳዊት
በአገራችን ትላልቅ አገልግሎት ሰጪዎች ከሚባሉት መንግሥታዊ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን፣ የአዲስ አበባና የክልል የውሃና ፍሳሽ አገልግሎት መሥሪያ ቤቶች እና የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ተጠቃሽ ናቸው፡፡
"ኢትዮጵያ ከኦርጋኒክ ግብርና የምታገኘው ምንዛሪ በ10 እና በ20 በመቶ ማደግ አለበት"
አቶ አዲሱ አለማየሁ
አቶ አዲስ አለማየሁ የኢትዮጵያን አሶሴሽን ኦፍ ኦርጋኒክ አግሪካልቸር የቦርድ አባልና ሥራ አስኪያጅ ናቸው፡፡ ከማህበሩ መስራቾች መካከልም አንዱ ናቸው፡፡ በማህበራቸው የሥራ እንቅስቃሴ ዙሪያ ዳዊት ታዬ አነጋግሯቸዋል፡፡
(ሰውየው ራሳቸው ያለውን ሁኔታ ከአንድ ባለሥልጣን ጋር ሊነጋገሩበት ፈልገዋል፡፡ ባለሥልጣኑም የሰውየው ችግር ምንድነው? ያለው ሁኔታስ ወዴት እያመራ ነው? የሚለው ጉዳይ ስላሳሰባቸው ከዋናው ሰውዬ ጋር ለመነጋገር ፈልገዋል፡፡ ባለሥልጣኑ ክቡር ሚኒስትሩ ናቸው፡፡ ሰውዬው ደግሞ ዋነኛው ባለሃብት ናቸው)
ልጅነት
በሔኖክ ያሬድ
"ያ ልጅነት በጊዜያቱ ደስ ማለቱ" አንጎራጉር ነበር ያኔ ስሰማ የነበረው የድምፃዊው ዜማ ዛሬ የተከሰተልኝ ከሪደርስ መጻሕፍት መደብር ስወጣ ነበር፡፡ ልጅነትን የሚያስታውስ በተለይም የእኔን የልጅነት ዘመን በ1950ዎቹ መካተቻና በ1960ዎቹ መጀመሪያ ዘመን መቼቱን ያደረገ በልብ ወለድ መልክ የቀረበ መጽሐፍ መመልከቴ ነበር፡፡
አርባ አንድ ዓመታት በአሰጋጅነት
በሠለሞን ጐሹ
ሼህ መሐመድ ኑር ያሲን በሰሜን ወሎ ዞን ሐብሩ ወረዳ መርሳ ከተማ የሚገኘው ሃረመይን መስጊድ ኢማም ናቸው፡፡ በስራቸው ላይ በመርሳ ከተማ ብቻ ከ1960 ዓ.ም. ጀምሮ እንደቆዩ ይናገራሉ፡፡ በዋና አሰጋጅነት ከ41 ዓመት በላይ ቆይተዋል፡፡
ኦቫሪ ተተክቶላት መውለድ የቻለች...
ኦቫሪ ተተክቶላት መውለድ የቻለች የመጀመሪያዋ እናት
የሴቴ እንቁላል ማምረቻ አካል (ኦቫሪ) በቀዶ ሕክምና የተተካላት በዓለም ላይ የመጀመሪያዋ የሆነችው እናት በሰላም መገላገሏ ሴት ልጅ ተዓምር ማሰኘቱን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
"ዲያስፖራው የበለጠ እንዲሰራ...
"ዲያስፖራው የበለጠ እንዲሰራ የመንግሥት እገዛ ያስፈልገዋል"
በዳዊት ታዬ
አቶ ጥላሁን ጌታቸው ከ22 ዓመታት በላይ በስደት ቆይተው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡ የ42 ዓመት ጐልማሳ የሆኑት አቶ ጥላሁን ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ናቸው፡፡
እንዲሸፍቱ የተገደዱ ልቦች
በምሕረት አስቻለው
ጠባቡ ቢዝነስ ሴንተር ዲቪ በሚሞሉ ሰዎችና እነሱን ለማስተናገድ ወዲያ ወዲህ በሚሉ ሠራተኞቹ ተጨናንቋል፡፡ ከቀኑ አምስት ሰዓት ገደማ ላይ ሃያ ሁለት አካባቢ ከሚገኘው አለም ቢዝነስ ሴንተር ስንደርስ፣ ፎርም የተቀበሉና መቀመጫ ያገኙ ተስተናጋጆች ቁጭ ብለው የዲቪ ፎርም ሲሞሉ መቀመጫ ያላገኙት ደግሞ ቆመው በመጠባበቅ ላይ ነበሩ፡፡ ወደ ውስጥ ለመግባት ሞከርን፡፡ የዲቪ ፎርም በመሙላት ላይ የነበሩት (ሁሉም ማለት ይቻላል) ወጣቶች ነበሩ፡፡ ጠጋ ብለን ልናናግራቸው እንደምንፈልግ የጠየቅናቸው ፎርሙን ሞልተው ከጨረሱ በኋላ እንደሚያነጋግሩን ቃል ገቡልን፡፡ እኛም ቢዝነስ ሴንተሩ ደጃፍ ላይ ቆመን መጠባበቅ ጀመርን፡፡
መቻቻልና ፣ተው ቻለው ሆዴን ' ምን አንድ አረጋቸው?
አንዳርጋቸው ተሻገር
በየዓመቱ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካኝነት ተሰይመው አባል አገራት እንዲያከብሯቸው ከተወሰኑ የዓለም ወይም ኢንተርናሽናል "ቀን" ከሚባሉት መካከል በዚህ በያዝነው ወር ከ"ተከበሩት" ወይም ተከበሩ ተብለው በአገር ውስጥ ዜና ሲነገሩ ከፊሎቻችን በጨረፍታ ወይም ድንገት ሌሎች ደግሞ በቁም ነገር ሆን ብለው የሰማነው የ"መቻቻል" ቀን የተባለውን ነው በእንግሊዝኛው ቶለራንስ ይሉታል፡፡ ከአማርኛው "መቻቻል" ጋር ወይም ከሱ በተጨማሪ የእንግሊዝኛውን "ቶለራንስ" ማንሳት የተገደድኩበት ምክንያት ከእንግሊዝኛው ይበልጥ የአማርኛው ቃል በጣም የሚያሳጣው መደበቅ የማይቻለው "ሰብዓዊ መብተኛ" (ሂውማን ራይትስ ፍሬንድሊ) ያልሆነ የሚተናነቀው "አሉታዊ" ነገር ስላለው ነው፡፡ የእንግሊዝኛው "ቶለራንስ"ም ቢሆን የጠራ የነጠረ ስለመሆኑ፣ አለዚያም በሌላ አነጋገር ያልተበረዘ ያልተከለሰ ነው ተብሎ የጤንነት ወይም የጤናማነት የንጽህና ማረጋገጫ የሚሰጠው አይደለም፡፡
ኮሜርስ መግባት ማለት መራብ ማለት ሆነ?
"ኮሜርስ (ንግድ ሥራ ኮሌጅ) መግባት በራሱ መራብ፣ መቸገር ማለት እንደሆነ ነው የሚገባኝ፡፡ ወንዶችስ ወንድ ስለሆኑ ጎዳና ላይም ሊያድሩ ይችላሉ፡፡ የሚያድሩም አሉ፡፡ እኛ ሴቶች ግን ይሄንን ብናደርግ ራሳችንን አደጋ ላይ መጣል ይሆናል፡፡ ስለዚህ እየተራብን የምንበላው ሳይኖረን ለምንኖርበት ቤት ኪራይ እየከፈልን መኖር የግድ ነው፡፡ በኪራይ እየተኖረም ለሴቶች ችግሩ ብዙ ነው፡፡ አብረን ወጭ እየተጋራን እንኖራለን ብለው ከወንዶች ጋር ከተከራዩ ሴቶች መካከል አንዷ ለመመረቅ ሁለት ወር ሲቀራት አብሯት ከተከራየ ልጅ ፀንሳ ወደ ቤተሰቦቿ መመለሷን አውቃለሁ፡፡ እስካሁንም አልመጣችም፡፡" ይሄንን ያለችን የክፍለ ሃገር ልጅ የሆነችውና በንግድ ሥራ ኮሌጅ የሦስተኛ ዓመት ተማሪ የሆነችው ቢ (ማንነቷን ለመደበቅ ሲባል ስሟ በምህፃረ ቃል ተገልጿል) ናት፡፡
በድህነታችን ላይ ነጻ ያልሆነ ሚዲያ መደረብ አንችልም
ከበደ ፍሬው
የፕሬስ ነጻነት የሰብአዊ መብት መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ የእውቀትና የመታወቅ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ማንም በዚህ ላይ የተለየ ሃሳብ፣ ሌላ ግኝት አለኝ የሚለው የለውም፡፡ የፕሬስ ነጻነት ራሱ የተለየ ብቻ ሳይሆን ያልተለመደ፣ የማይወደድ፣ የሚያስደነግጥ፣ የሚያስፈራ ሃሳብ የሚፈቅድ፣ የማይከለክል ሆኖ እያለም ጭምር ነው፡፡ ከዚህም የተነሳ ነው ኢትዮጵያ በንጉሠ ነገሥቱም በወታደራዊው መንግሥትም ዘመን በነበሩት ሕገመንግሥቶች ጨምሮ በመላው ዓለም ዙሪያ ያሉና የነበሩ መንግሥታት ሕገመንግሥቶች ወይም አቻ ህጎች ከዚህ ጉዳይ ፈቀቅ ወይም ፈንገጥ የሚል የተለየ ወይም የተቃረነ ነገር የሌላቸው ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያም ጨምሮ በመላው ዓለም ዙሪያ 60ኛ ዓመቱን የሚያከብረው የዩኒቨርሳል ዲክላሬሽን ኦፍ ሂውማን ራይትስ መሰረታዊ ድንጋጌዎች ባጠቃለለ እና አንቀጽ 19 በተለይ የብዙ አገሮች ሕገመንግስቶች የቋንቋ የቃል አግባብ እና የይዘት ቅድመ መሰረት የሆኑት ከዚህ የተነሳ ነው፡፡ ይህንኑ በምስክርነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡
የህፃናት ህገ ወጥ ዝውውር
የህጻናት ህገ ወጥ ዝውውር እድሜአቸው ከ18 ዓመት በታች በሆኑ ህፃናት ላይ የሚፈፀም በህፃናት ላይ ከሚደርሱ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች አንዱ ሲሆን ህፃናትን ለመበዝበዝ ወይም መጠቀሚያ ለማድረግ ታስቦ ወይም አላማ አድርጎ በመመልመል፣ ከቦታ ወደ ቦታ፣ ሀገር ውስጥ ማጓጓዝ ወይም ከሀገር ውጭ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት ወይም ከአንድ ሀገር በማስወጣት ወደ ሌላ ሀገር መወሰድ ወይም ለሌላ ወገን በማስተላለፍ ወይም በመደበቅ ወይም በመቀበል የድርጊቱ ፈፃሚዎች ላቀዱት የብዝበዛ ዓይነት ህፃናቶቹን ማዋል ማለት ነው፡፡
በ1911 ዓ.ም የበሽታ መቅሠፍት በኢትዮጵያ ላይ ወርዶ ብዙ ሰው አለቀ፡፡ በሽታው አዲስ አበባ ደርሶ በጣም የታወቀው በኅዳር ወር ስለሆነ በሕዝብ ቃል "የኅዳር በሽታ" የሚል ስም ወጣለት፡፡ ፈረንጆች ግን የበሽታውን ስም ግሪፕ ብለውታል፡፡ በአገራችንም አንዳንድ ሰዎች "ቸነፈር" ብለውት ነበር፡፡
ለልጁ ሲል ሕይወቱን የሚፈልገው ወንድወሰን
በትዕግሥት ዘሪሁን
ወንድ ወሰን ፈረደ ተወልዶ ያደገው አዲስ አበባ ውስጥ ነው፡፡ ለበርካታ ዓመታት በጠቅላይ ቤተክህነት የደህንነት ጥበቃ አባል ሆኖ ሰርቷል፡፡ በዚህ የሥራ ዘርፍ ላይ እያለም ከሦስት ልጆችና ባለቤቱ ጋር ጥሩ የሚባል ኑሮ ይኖሩ እንደነበር ገልፆልኛል፡፡ ከአራት ወር በፊት ጀምሮ ግን ኑሮውና ሕይወቱ ተቀይሯል፡፡
ድክመትን በመስተዋት
በኃይሉ አስፋው ገብረየስ
የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ፣ የስፔን ላ ሊጋ፣ የኢጣሊያ ሴሪ አ እንደ ጅብ ጥላቸውን የጣሉበት የኢትዮጵያ እግር ኳስ ስፖርት ችግር ከመባባስ በስተቀር ሲፈታ አይታይም፡፡ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚባለው በኢትዮጵያ የአሸናፊዎች አሸናፊ ዋንጫ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቡድን በጨዋታና በውጤት የበላይነት በውድድር ሜዳ፣ የኢትዮጵያ ቡና ቡድን የውድድር ዝግጅት እና ሥነ ሥርዓት ኮሚቴ በቢሮ በሰጠው ውሳኔ ያስመዘገቡት ድል በዳኝነት የሕግ አተረጓጎም፣ በተጨዋች ተገቢነትና በስፖርታዊ ጨዋነት ዙሪያ ያስነሳው ውዝግብ እና የስፖርት ጋዜጠኞች ያዘመመ አስተያየት ያልታደለውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ስፖርት የበለጠ በማቁሰል ጠባሳውን ጥሎ አልፏል፡፡
ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ወደ ስልጣን ሲመጡ በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ወሳኝ በሆኑ የሀላፊነት ቦታዎች ይሾማሉ፣ ከ2.6 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የፌዴራል መንግሥቱ ሰራተኞች ግን የያዙትን ሥራ ይዘው ይቀጥላሉ፡፡
Dear Visitors, we are currently moving our web site to a new server to better serve you with fast and accessible site. While we are doing this you might find broken links and missing images. Therefore, we would like to ask you to wait patiently until we restore our site to its original state with all missing images and a new streaming audio/video service.
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |
Share your thought and ideas with others on our public forum. Just register here and participate on our new and improved forum. Note that all members of the old version forum have to register again to post on the new version forum.