Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow ኤሌክትሪክ የሚቋረጥበት ፕሮግራም...
ኤሌክትሪክ የሚቋረጥበት ፕሮግራም... Print E-mail
Wednesday, 30 April 2008
ኤሌክትሪክ የሚቋረጥበት ፕሮግራም በአንድ ሰዓት ከፍ አለ  

በጋዜጣው ሪፖርተር

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ትላንት ይፋ ባደረገው የአንድ ወር ፕሮግራም የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጥባቸው ቀናት ፕሮግራም በአንድ ሰዓት አራዘመ፡፡ ከፈረቃ ውጪ የሚደርስ የኃይል መቋረጥ ችግሮችን ለመቅረፍ ኮርፖሬሽኑ ጥረት እያደረገ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

አቶ ሰንደቁ አርአያ የኮርፖሬሽኑ ሕዝብ ግንኙነት ሥራ አስኪያጅ ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለፁት ኮርፖሬሽኑ የገጠመውን የኃይል እጥረት ለማስተካከል በያዝነው ወር ባወጣው የፈረቃ እደላ ፕሮግራም መሠረት እስከ ሰኔ 30/2000 መድረስ ስለማይቻል ኃይል የሚቋረጥባቸው ቀናት ምንም ዓይነት ለውጥ ሳይደረግ፤ ከጠዋቱ 1 ሰዓት እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት የነበረውን እስከ 3 ሰዓት እንዲራዘም ወስኗል፡፡ በዚሁ መሠረት አዲሱ ፕሮግራም ከሚያዚያ 20 እስከ ግንቦት 30 ቀን 2000 የሚሠራበት ይሆናል፡፡

"ከፈረቃ ውጪ በተለያዩ አካባቢዎች በተደጋጋሚ ለምን ኃይል ይቋረጣል?" በሚል ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ ችግሩን ለመቅረፍ የኮርፖሬሽኑ የቴክኒክ ቡድን እያጠና የመፍትሄ ሃሳብ እያቀረበ ነው፡፡ ኮርፖሬሽኑ ከፈረቃ ውጪ የኃይል መቋረጥን መፍትሄ ለመስጠት ብርቱ ጥረት እያደረገ ነው" ሲሉ ገልፀዋል፡፡

አንዳንድ የኮርፖሬሽኑ ደንበኞች በበኩላቸው ኮርፖሬሽኑ በይፋ በጋዜጣ ካወጣው ፕሮግራም በተጨማሪ በማንኛውም ቀንና ሰዓት የኃይል መቋረጥ በተደጋጋሚ ማጋጠሙ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ችግሩም ከዚህ በፊት ያልነበረ ከመሆኑ አንፃር ሲታይ ሆን ተብሎ የሚደረግ ይመስላል በማለት ቅሬታቸውን ገልፀዋል፡፡

በተያያዘም ከሚያዚያ 22 - 26 ቀን 2000 ዓ.ም ለሚካሄደው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድሩ በሚካሄድባቸው ዋና ዋና ቦታዎች ኃይል እንደማይቋረጥ አቶ ሰንደቁ ጠቁመው ስፖርተኞች ባረፉባቸው ሆቴሎች ኃይል በሚቋረጥባቸው ቀናት ዲዝል ጄኔሬተሮች እንዲጠቀሙ

የቴክኒከ እገዛ ለመስጠት የኮርፖሬሽኑ ባለሙያዎች ተንቀሳቅሰው አጥጋቢ ውጤት ማግኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡

ከሐራምቤ ሆቴል በስተቀር ሁሉም ሆቴሎች የጄኔሬተር ተጠቃሚ መሆናቸውን ማረጋገጥ መቻሉንም አስረድተዋል፡፡
 
< Prev   Next >