Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow በማደጎ የሚወሰዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ጨምሯል
በማደጎ የሚወሰዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ጨምሯል Print E-mail
Wednesday, 30 April 2008
ከጋዜጣው ሪፖርተር

በማደጎነት የሚወሰዱ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ባለፈው ዓመት ብቻ 71 በመቶ መድረሱን አሶሽየትድ ኘሬስ ዘገበ፡፡

"ኢትዮጵያ በግልፅነት ችግር ምክንያት አብዛኛዎቹ በማደጎነት የሚወስዱበት ሃገር ሆናለች" ሲል በማደጎ የሚወሰደውን ንግግር ጠቅሶ የዜና ወኪሉ ዘግቧል፡፡

በአዲስ አበባ የአሜሪካ አሳዳጊዎች በከተማዋ ሆቴሎች የሚታዩ መሆናቸውንም ጠቅሷል፡፡

ከኢትዮጵያ በማደጎነት ለመውሰድ 30"000 የአሜሪካን ዶላር እንደሚፈጅና በአሜሪካ ከሚከፈለው ግን አነስተኛ መሆኑን በዜናው ተመልክቷል፡፡

በተያያዘ ዜና ቬትናም ዜጎቿ ወደ አሜሪካ በማደጎነት እንዳይሄዱ ከልክላለች፡፡ ክልከላው የፀናው አሶሽየትድ ኘሬስ ከቬትናም ወደ አሜሪካ በማደጎ የሚወሰዱ ልጆች ሕፃናቱ ለሆስፒታሎች እንደሚሸጡ፣ ጫና እንደሚደረግባቸው፣ በየመንደሩ ደላሎች እያሰሱ እንደሚወስዱዋቸው፣ ከአያቶቻቸው ጋር የሚያድጉ ሕፃናትን የእናታቸውን ስም ሳይነግሩ እንደሚልኳቸው ከዘገበ በኋላ ነው፡፡
 
< Prev   Next >