Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow በንፁሃን መሞት የሚደሰቱ
በንፁሃን መሞት የሚደሰቱ Print E-mail
Wednesday, 30 April 2008
በሪፖርተር ጋዜጣ ሚያዚያ 19 ቀን 2000 በ"እኔ የምለው" ገጽ ላይ "የስሜት ማዕበል ለምን ያናውጸናል?" በሚል ርዕስ የቀረበው ጽሁፍ አንብቤያለሁ፡፡

የአንድ ባለሃብት ንብረት በሆኑ ሁለት የነዳጅ ማዲያዎች ላይ ያነጣጠሩ ፍንዳታዎች ንጹሀንን ዜጎችን ለህልፈተ ሕይወት ዳርገዋል፡፡ ማደያዎቹን ለማጋየት የተጠመደው ፈንጂ ድሆችና ሰላማዊ ሰዎችን ጎድቷል፡፡ ባለሃብቱ በዚህ ተደናግጠው እያካሄዱ ያሉትን ልማት እንዲያቆሙ ለማድረግ የተሞከረ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህን የመሰለ ጥፋት የሚፈጽሙ በድርጊታቸው ሊያፍሩ እንጂ ሊደሰቱ አይገባም፡፡ ሕብረተሰቡ ሕዝብ በሚሰበሰብባቸው ቦታዎች እያንዳንዱ እንቅስቃሴ መከታተል ያስፈልጋል፡፡ ሰውን በጅምላ በማጥፋት የሚረኩ ሰዎች ስላሉ ምንጊዜም መዘናጋት አያስፈልግም፡፡ በንፁሃን ላይ ያነጣጠሩ ከእንደዚህ ዓይነት ድርጊታቸው ሊቆጠቡ ይገባል፡፡ በፈንጂ የሰውን ልጅ በማቃጠል የሚገኝ አዎንታዊ ነገር የለም፡፡ ሰውን መግደል በሰውም በፈጣሪ ዘንድም የተወገዘ ነው፡፡

(ፈለቀ ደሳለኝ፣ ከመርካቶ)
 
< Prev   Next >