Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow ኢትዮጵያ በኳታር ላይ የወሰደችው...
ኢትዮጵያ በኳታር ላይ የወሰደችው... Print E-mail
Wednesday, 30 April 2008
ኢትዮጵያ በኳታር ላይ የወሰደችው እርምጃ ኤርትራ ተቃወመች

በጋዜጣው ሪፖርተር

የኤርትራ ዋነኛ ሽርካ የሆነችው ኳታር በቀጣናው ሽብርተኝነትን እያስፋፋች ነው በማለት ኢትዮጵያ የወሰደችው የግንኙነት መቋረጥ እርምጃ ኤርትራን ማስደንገጡን ኤ.ኤፍ.ፒ የተባለው የዜና ወኪል ዘገበ፡፡

የኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጉዳዩን አስመልክቶ ለኤ.ኤፍ.ፒ በሰጠው መግለጫ "እርምጃው በጣም አስደንጋጭ ነው" ብለዋል፡፡ የመግለጫው መከራከሪያ ነጥብ ኢትዮጵያ የወሰደችው ውሳኔ ኤርትራ በተለይ "ወደ ሶማሊያ የሚጎርፈው የኳታርና የሊብያ ድጋፍ ታጓጉዛለች" በሚል ክስ አሜሪካ በአሸባሪዎች ተርታ ከማስፈርዋ የተነሳ እንደሆነ ያትታል፡፡

ባለፈው ሳምንት ኢትዮጵያ የዕምቅ ተዋጊዎችና የሶማሊያ አክራሪዎች ትረዳለች በማለት ኳታርን የከሰሰች ሲሆን ከአገሪቱ ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማቋረጧ ይታወሳል፡፡

ኤርትራ በበኩሏ ኢትዮጵያ በሶማሊያ የአገር ውስጥ ፖለቲካ ጣልቃ መግባትዋንና የአገሪቱን ሰላም ማመሷን ትከሳለች፡፡  

ባለፈው ረቡዕ የኳታር ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እርምጃውን አስመልክተው በሰጠው አስተያየት በውሳኔው መገረሙና መሠረት የሌለው ውንጀላ መሆኑን በመተቸት፣ "የአገሪቱ የተሳሳተ ፖሊሲ ነፀብራቅ ነው" ብለዋል፡፡

ኳታር ከምትረዳቸው የዕምቅ ተዋጊዎች ወይም አሸባሪዎች መካከል ኦብነግ የሚገኝበት ሲሆን ቡድኑ ኢትዮጵያ በአገሪቱ ላይ በወሰደችው እርምጃ ማዘኑንና ተቃውሞውን መግለፁ ይታወሳል፡፡
 
< Prev   Next >