Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow ባህሬን ከኢትዮጵያ የቁም ከብት...
ባህሬን ከኢትዮጵያ የቁም ከብት... Print E-mail
Wednesday, 30 April 2008
Imageባህሬን ከኢትዮጵያ የቁም ከብት መግዛት ልትጀምር ነው

በባህሬን የተከሰተውን የቀይ ስጋ እጥረት ለማስወገድና በገበያ ውስጥ ያለውን ችግር ለማርገብ ከኢትዮጵያ የቁም ከብት ለመግዛት በዝግጅት ላይ እንደሆነች አስታወቀች፡፡
ከባህሬን የንግድና ኢንዱስትሪ ም/ቤት (ቻምበር) የወጣ መግለጫ እንዳመለከተው፣ በባህሬን ውስጥ የተከሰተውን የቀይ ሥጋ እጥረትን ለማስወገድ ከኢትዮጵያ የቁም ከብት መግዛት የተሻለ አማራጭ ነው፡፡

ባለፈው ሳምንት ወደ ባህሬን ከሄደው የኢትዮጵያ የንግድ ልዑካን ጋር መወያየታቸውንና ለሥጋ የሚሆኑ ከብቶችን ለማግኘት የሚያስችል ስምምነት ላይ መደረሱን የንግድ ም/ቤቱ ምክትል ሊቀመንበር ኢብራሒም ዘይናው ገልፀዋል፡፡

ምክትል ሊቀመንበሩ በውይይቱ ላይ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የእንስሳት ሃብት ያላት አገር መሆኗን ለመረዳት መቻላቸውንና የሚፈልጉትን ያሀል ምርት እንደሚያገኙ እምነት እንዳላቸው ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ በግምት 100 ሚሊዮን የሚደርስ የእንስሳት ሃብት አላት ብለዋል፡፡

ብዙ አገሮች የባህሬንን የቀይ ሥጋ እጥረትን ተከትሎ አማራጭ እያቀረቡ ሲሆን ኢትዮጵያ በፍጥነት በዕድሉ ተጠቃሚ መሆን እንደሚኖርባትም ተገልጿል፡፡
 
< Prev   Next >