Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር...
የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር... Print E-mail
Sunday, 04 May 2008
Imageየግብርናና ገጠር ልማ ሚኒስቴር የ100 ዓመት ጉዞ

በታምሩ ጽጌ

የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር አንድ መቶኛ ዓመቱን ሚያዚያ 24 ቀን 2000 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል በሴባስቶፓል ሲነማ አዳራሽ አክብሯል፡፡

በዓሉን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስትር አቶ አዲሱ ለገሠ በይፋ መርቀው ከፍተዋል፡፡

ሚኒስትሩ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ መቶኛ ዓመት በዓሉን በማስመልከት ያዘጋጀውን ኤግዚቢሽን መከፈት ይፋ ሲያደርጉ ባደረጉት ንግግር፣ “በዓሉን ልዩ የሚያደርገው የሚሌኒየም በዓል በሚከበርበትና በአገራችን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢኮኖሚያችን ዘርፍ ከፍተኛ ዕድገት እያስመዘገበ ያለበት ወቅት መሆኑና ዕድገቱን ለማስመዝገብ ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈልንበት የግንቦት 20 በዓል ዋዜማ ላይ መከበሩ ነው” ብለዋል፡፡

ለድህነትና ለኋላ ቀርነት የዳረገንን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መዋቅር ከሥር መሠረቱ የሚንድ በሕዝቦች ተሳትፎና ትግል የተረጋገጠ ሕገ መንግሥት ባለቤት መሆናችንና በዚሁ ሕገ መንግሥት ተረጋግጠው የወጡ ፖሊሲዎችና መብቶች በመኖራቸው ዛሬ ዕድገትን እያየን መሆኑን ሚኒስትሩ አረጋግጠዋል፡፡

ሴክተሩ በገበያ የሚመራ ግብርና መር በመሆኑ ዓለምንም የሚያነጋግር የኢኮኖሚ መሠረት መሆኑን፣ በአገራችንም በርካታ አርሶ አደሮች ሕይወታቸውን እየለወጡበት መሆናቸውን አቶ አዲሱ ተናግረዋል፡፡
 
< Prev   Next >