Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
May 18th
Home arrow Sections arrow የዕንቁ መጽሔት አሣታሚና ሦስት የሥራ...
የዕንቁ መጽሔት አሣታሚና ሦስት የሥራ... Print E-mail
Wednesday, 07 May 2008
የዕንቁ መጽሔት አሣታሚና ሦስት የሥራ ባልደረቦቻቸው የጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀባቸው

በታምሩ ጽጌ

በአለማየሁ አሣታሚ ድርጅት ሥር በየወሩ እየታተመ የሚወጣው የዕንቁ መጽሔት አሣታሚ፣ ምክትል አዘጋጅና ሦስት ተባባሪ ሠራተኞቻቸው ላይ ትናንት  ፖሊስ የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቆ ተፈቀደለት፡፡

ፖሊስ አሣታሚውን አቶ አለማየሁ ማህተመ ወርቅ፣ ሲሳይ ወርቁ፣ ሰሎሞን መኮንንና ኢሣያስ (የታክሲ ሾፌር) ሚያዚያ 24 ቀን 2000 ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ሰዓት አካባቢ በብራና ማተሚያ ቤት ያሳተሙትን አሥር ሺ ዕንቁ መጽሔት ለመውሰድ ሲሄዱ ከነመጽሔቱ በቁጥጥር ሥር አውሎ እንዳሰራቸው የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈቃዱ ማኅተመ ወርቅ ለሪፖርተር ጋዜጣ ገለፀዋል፡፡

መጽሔቱን ለክልሎችና ለአዲስ አበባ ለማከፋፈል ወደ ማተሚያ ቤቱ (ብራና) ሲገቡ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሠራተኞችም ሆነ እሳቸው ባላወቁት ምክንያት ለሦስት ቀናት ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ፖሊስ በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ልደታ ክፍለ ከተማ ምድብ ችሎት አቅርቦ የ14 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ ጠይቆ እንደተፈቀደለት ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡

ሚያዚያ 25 ቀን 2000 ዓ.ም ለገበያ ሊበቃ የነበረው ዕንቁ መጽሔት በአብዛኛው የያዘው መጣጥፍ ከፊት ሽፋኑ ጭምር፣ በቅርቡ ክስ ተመስርቶበት የዋስትና መብት ተከልክሎ ማረሚያ ቤት የሚገኘው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሣሁንን (ቴዲ አፍሮ) መሆኑንና ሌሎችንም መጣጥፍ እንደያዘ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በቁጥጥር ሥር ውለው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በእስር ላይ የሚገኙት የመጽሔቱ ሠራተኞች ለግንቦት 11 ቀን 2000 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን፣ በዕለቱ ችሎት ሲቀርቡ ቤተሰብና ጋዜጠኞች እንዳይገቡ ተከልክሎ በጽ/ቤቱ በኩል ጊዜ ቀጠሮ እንደተጠየቀባቸው ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ 
 
< Prev   Next >