| 4000 መምህራን ለምርጫ ሥራ... |
|
|
| Thursday, 10 January 2008 | |
|
4000 መምህራን ለምርጫ ሥራ መሰማራታቸው ትምህርቱን ይጐዳል በአዲስ አበባ ከተማ በሚካሄደው የወረዳ፣ የቀበሌና የማሟያ ምርጫ 4ሺ መምህራኖች መመልመላቸው የትምህርት ሂደቱን ይጐዳል በሚል የክፍለ ከተማ የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ተቃወሙት፡፡ የክፍል ከተማ የትምህርት ሥልጠና ፅህፈት ቤት (የክፍለ ከተማ የትምህርት ቢሮ) ኃላፊዎች ተቃውሟቸውን ያቀረቡት በጋራ ባደጉት ስብሰባ ነው፡፡ የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ መምህራኑ በብዛት ወደ ምርጫ ሥራ እንዲገቡ መደረጉ በትምህርቱ ሥራ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሊያደርስ እንደሚችል ኃላፊዎቹ አስጠንቅቀዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ትምህርት ማስተባበሪያ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ካሳሁን ጣሰው የክፍለ ከተማ ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች ባቀረቡት መሠረት ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር ንግግር እንደሚደረግ ለሪፖርተር ገልፀዋል፡፡ የክፍለ ከተማ የቢሮ ኃላፊዎች ለምርጫ ሥራ የሄዱባቸውን መምህራን ብዛት በየዘርፉና በየደረጃው ለይተው እንዲያቀርቡ መጠየቃቸውም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ የምርጫ ሥራ ሁሉም ወገኖች መሰለፍ አለባቸው ያሉት ኃላፊው የትምህርት ሥራ ላይ ችግር የሚፈጠር መሆኑ ታይቶ ማስተካከያ እንዲደረግበት ይደረጋል ብለዋል፡፡ በአዲስ አበባ በቅድመ መደበኛ 4..534፣ በአንደኛ ደረጃ 14..549 በሁለተኛ ደረጃ 4..565፣ መምህራኖች ሲኖሩ የተጠቀሰው ቁጥር የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ቤቶችን አያካትትም፡፡ በአሰግድ ተፈራ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |