| ሕዝቡ የልማት ጥሙን ካረኩለት ይተባበራል |
|
|
| Wednesday, 07 May 2008 | |
|
አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የአፍሪካ መዲና ናት፡፡ የበርካታ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መናኸሪያ ናት፡፡ ይሁን እንጂ በልማትና በተወሳሰቡ ችግሮች የተዘፈቀች ናት፡፡ ከመሬት ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ሙስና የሚፈጸምባት ሆናለች፡፡ ድህነት በጣም ተንሰራፍቶባታል፡፡ በዚህ ሁኔታ ላይ የምትገኘውን አዲስ አበባን በከንቲባነት ለማስተዳደር ብልህነትን፣ አርቆ አስተዋይነትን፣ ቆራጥነትን፣ ከሙስና መጽዳትን፣ ብቃት ያለው አመራር ሰጪነትን ያስፈልጋል፡፡ ከተማን የማስተዳደር ልምድ ያካበተ ሰው ሊሆን ይገባል፡፡
በሪፖርተር ጋዜጣ ሚያዚያ 26 ቀን 2000 እትም ፖለቲካ ገጽ "ኩማ ወደ ማዘጋጃ ቤቱ እያቀኑ ነው" በሚል ርዕስ ጽሑፍ ወጥቷል፡፡ አቶ ኩማ ብዙ ሥራና ኃላፊነት እንደሚጠብቃቸው ከወዲሁ መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከሁሉ አስቀድሞ ግን ቢሯቸውን ለጋዜጠኞች ክፍት ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ በዚህ በኩል ከንቲባ ብርሃነ ደሬሳን በጥሩ አብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ ከዚህም ሌላ በሕዝቡ መሃል እየተገኙ ችግሩንና ብሶቱን ሊረዱለትና መፍትሄም ሊፈልጉለት ይገባል፡፡ በውዝፍነት የሚጠብቋቸውን ጉዳዮች በአፋጣኝ የመፍታትና ከሕዝብ ጋር የመቀላቀል ችሎታ ማዳበር አላባቸው፡፡ በተዛባ መልኩ የተከናወነው የሠራተኛ ቅነሳ በአስተዳደሩ ከፍተኛ የሆነ የባለሙያ እጥረት እንደፈጠረ እየታየ ነው፡፡ ለእነዚሀ ችግሮች መፍትሄ መስጠት የአቶ ኩማ ሥራ ይሆናል፡፡ ሕዝቡ የሚፈልገው ልማት ነው፡፡ መልካም አስተዳደር ነው፡፡ አድሎአዊነት የሌለበት ፍትሃዊ ውሣኔ ነው፡፡ ይህን ካሟሉለት ሕዝቡ ይደግፋቸዋል፤ ይተባበራቸዋል፡፡ (ፈለቀ ኃይሉ፣ ከአየር ጤና) |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |