Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 06th
Home arrow Sections arrow የደቡብ ክልል ምክትል ኘሬዚዳንት...
የደቡብ ክልል ምክትል ኘሬዚዳንት... Print E-mail
Sunday, 11 May 2008
የደቡብ ክልል ምክትል ኘሬዚዳንት በግምገማ ከኃላፊነታቸው ተነሱ

በጋዜጣው ሪፖርተር

የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ምክትል ኘሬዚዳንትና የአቅም ግንባታ ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ ፀጋዬ ማሞ “በስነ ምግባር ችግር” ተገምግመው ከኃላፊነታቸው ተነሱ፡፡
አቶ ፀጋዬ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉ ሲሆን ከሥነ ምግባር ችግር ጋር በተያያዘ ሰሞኑን በተደረገ ግምገማ የቀረበባቸውን ድክመት መቀበላቸውን የክልሉ ምንጮች አስረድተዋል፡፡ በዚህም ሳቢያ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ተወስኗል፡፡

አቶ ፀጋዬ የደኢህዴን እና የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ነበሩ፡፡ በተያያዘም ሰሞኑን በተካሄደው የደኢህዴን ግምገማ ላይ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ ለብአዴን ተፅዕኖ የፓርቲውን አባላት አጋልጠዋል፤ በሚል መገምገማቸውን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

ፓርቲው በሌሎች ተጨማሪ ሦስት የክልሉ የሥራ ኃላፊዎች ላይ ተመሳሳይ እርምጃ የወሰደ መሆኑም ታውቋል፡፡

 
< Prev   Next >