Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 20th
Home arrow Sections arrow የዳቦ አምራቾች ድጎማ እንዲደረግላቸው...
የዳቦ አምራቾች ድጎማ እንዲደረግላቸው... Print E-mail
Sunday, 11 May 2008
የዳቦ አምራቾች ድጎማ እንዲደረግላቸው ጥያቄ ለማቅረብ ተስማሙ

በቤዛዊት ሥዩም

የዳቦ አምራቾች የዱቄት ዋጋ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ በመሆኑ ዳቦን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ ድጎማ እንዲደረግላቸው ለንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጥያቄ ሊያቀርቡ ተስማሙ፡፡
የዳቦ አምራቾች ከጥራትና ደረጃዎች ባለሥልጣን በጋር የዳቦ ደረጃን ወጥ በሆነ ሁኔታ ለማውጣትና እየጨመረ ለመጣው የዱቄት ዋጋ መፍትሄ ለመፈለግ በተቋቋመው ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ተስፋዬ በሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለፁት፣ የስንዴ ዋጋ እየጨመረ በመምጣቱ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ ለማቅረብ እገዛ ያስፈልጋቸዋል፡፡

የዱቄት ዋጋ እየጨመረ በመምጣቱ ከጥራትና ደረጃዎች መዳቢ ባለሥልጣን ጋር በጋራ ባቋቋሙት ኮሚቴ ዳቦ አምራቾች በግብአትነት በሚጠቀሙበት ዱቄት ላይ የተለየ ድጎማ ወይም ዱቄትን ከአምራቾቹ በአነስተኛ ዋጋ በቀጥታ እንዲያገኙ የሚያስችላቸው ዕድል እንዲመቻችላቸው ጥያቄ እንደሚያቀርቡ ገልፀዋል፡፡

የዱቄት ዋጋ 820 ብር መድረሱን የገለፁት አቶ ተስፋዬ ዳቦ ቤቶች ያለባቸውን ወጪ በማስላት የዋጋ ማስተካከያ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል፡፡

ባለፉት ጊዜያት 50 ግራም ዳቦ ከ30 እስከ 35 ሳንቲም ይሸጥ እንደነበር ጠቁመው አሁን ባለው ዋጋ እያንዳንዱ ዳቦ ቤት ወጪውን በማመዛዘን የራሱን የዋጋ ስሌት እንዲያወጣ መስማማታቸውን ተናግረዋል፡፡ በዚሁ መሠረትም የአንድ ዳቦ አነስተኛ መጠን 50 ግራም በማድረግ ከ50 እስከ 60 ሳንቲም በመሸጥ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

የዋጋ ቁጥጥር ለማድረግ የተቋቋመው ግብረ ኃይል ለዳቦ ግብአት የሚውሉ ምርቶችን ዋጋ ባለመረዳት 50 ግራም ዳቦ በ20 ሳንቲም ሽጡ ብሎ ያስገድድ እንደነበርና በዚህ መሠረት የተዘጉ ዳቦ ቤቶች እንደነበሩ የገለፁት አቶ ተስፋዬ ጠቁመው እያንዳንዱ ዳቦ ቤት በሚያዋጣውና ኅብረተሰቡን በማይጎዳ በኩል የሚሸጥበት ሁኔታ እንዲመቻች ጠይቀዋል፡፡

የዳቦ አምራቾች ማኅበር ለመመስረት ከተመረጡት 15 የኮሚቴ አባላት ከጥራትና ደረጃዎች መዳቢ ባለሥልጣን ጋር በጋራ በመሆን በአዲስ አበባ በሚገኙ ዳቦ ቤቶች ባደረጉት የመስክ ጥናት አብዛኛዎቹ ዳቦ ቤቶች በጥራትና ደረጃዎች አነስተኛ የዳቦ መጠን ተብሎ ከተቀመጠው 50 ግራም ያነሰ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡

አብዛኛዎቹ ዳቦ ቤቶች ከ26.7 እስከ 49 ግራም ልዩነት የሚመዝን ዳቦ እንደሚያመርቱ በዳሰሳው የተገኘ ሲሆን ሁሉም ዳቦ ቤቶች ወጥ የሆነ ግራም እንዲኖራቸው ይህን ለማድረግ ፈቃደኛ ያልሆኑ ደግሞ ፈቃዳቸውን ሊነጠቁ አንደሚችሉም ተገልጿል፡፡

የግብአቶች ዋጋ መቀነስ ካልታየ ወደፊት አብዛኛዎቹ ዳቦ ቤቶች ሊዘጉ እንደሚችሉ ስጋታቸውን ገልፀዋል፡፡

 
< Prev   Next >