Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Friday
Aug 29th
Home arrow Sections arrow በአዲስ አበባ 32 ድልድዮች ከ4ዐዐ...
በአዲስ አበባ 32 ድልድዮች ከ4ዐዐ... Print E-mail
Friday, 11 January 2008

በአዲስ አበባ 32 ድልድዮች ከ4ዐዐ ሚሊዮን በላይ ወጪ እየተሠሩ ነው

ከመስቀል አደባባይ ቃሊቲ ያለው መንገድ ግንባታ ተጀመረ

በአዲስ አበባ ከተማ እየተገነቡ ካሉ የመንገድ ሥራዎች ጐን ለጐን ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የ32 ድልድዮች ግንባታ በመከናወን ላይ መሆኑ ተገለፀ፡፡ ከመስቀል አደባባይ ቃሊቲ ያለው መንገድ ግንባታም ተጀመረ፡፡

የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍቃዱ ኃይሌ ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደገለፁት በመገንባት ላይ ያሉት 32 ድልድዮች አዳዲስና ቀድሞ የነበሩትን ደረጃ የማሳደግ ሥራን ያጠቃልላል፡፡

የከተማውን እድገትና የትራፊክ ፍሰት ተከትሎ የድልድዮች ግንባታ ወሳኝ በመሆኑ አሁን ያለውና ወደፊት ሊኖር የሚችለውን የትራፊክ ፍሰት እና ብዙ ተሽከርካሪዎችን ለማስተናገድ የሚችሉ ድልድዮች በመገንባት ላይ ናቸው፡፡ አሁን እየተገነቡና ደረጃቸው እንዲያድግ እየተደረጉ ካሉት ጋር በጥቅሉ ከ29ዐ በላይ የሚሆኑ ድልድዮች መኖራቸውን የጠቆሙት አቶ ፍቃዱ፣ በቀጣይ ዓመታትም ከትራፊክ ፍሰቱ ጋር ተመጣጣኝ የሚሆኑ የድልድይ ግንባታዎች እንደሚከናወኑ አመልክተዋል፡፡

የድልድዮቹ ሥራ በአብዛኛው ለኮንትራክተሮች በተናጠል የሚሰጥ እንዳልሆነ ያመለከቱት አቶ ፍቃዱ፣ በተለያዩ የከተማው አካባቢዎች እየተገነቡ ካሉ መንገዶች ጋር በጥምረት የሚሠሩ ናቸው፡፡

በ2ዐዐዐ የበጀት ዓመት ባለሥልጣኑ ለመንገድ ጥገናና ለመሳሰሉት ሥራዎች ከተያዘለት ጠቅላላ በጀት 3ዐ በመቶው የድልድዮች ድርሻ ነው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከቃሊቲ እስከ መስቀል አደባባይ ድረስ ያለውን መንገድ በአዲስ መልክ ለመገንባት ጨረታውን ያሸነፈው የቻይናው ኩባንያ ቁፋሮ መጀመሩ ታውቋል፡፡

ለዚህ መንገድ ሥራ በመንገዱ ግራና ቀኝ ያሉ ቤቶች በመፍረስ ላይ ያሉ ሲሆኑ እየፈረሱ ካሉት ቤቶች መካከልም አብዛኛዎቹ የንግድ ቤቶች ናቸው፡፡ በተለይ በደብረ ዘይት መንገድ ጠመንጃ ያዥ አካባቢ ያሉ ንግድ ቤቶች በተሰጣቸው አጭር ጊዜ ቤቶቻቸውን እያፈራረሱ ንግዳቸውን ወደ ሌሎች አካባቢ በማዘዋወር ላይ ናቸው፡፡

ይህ መንገድ እየተገነባ ካለው የጐተራ ተላላፊ ድልድይ ጋር ተገጣጥሞ የሚሠራ ሲሆን ጠቅላላ ወጪውም ከ390 ሚሊዮን ብር በላይ ይሆናል፡፡

በዳዊት ታዬ

 
< Prev   Next >