Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Friday
Jul 04th
Home arrow Sections arrow "የአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ዳይሬክተሮች...
"የአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ዳይሬክተሮች... Print E-mail
Sunday, 13 January 2008

"የአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ዳይሬክተሮች ከሃላፊነታቸው የተነሱት ባቀረቡት መልቀቂያ መሰረት ነው"
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ

የአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ዳይሬክተሮች ከሀላፊነታቸው የተነሱት ራሳቸው ባቀረቡት መልቀቂያ መሰረት መሆኑን የባንኩ ፕሬዚዳንት ዋና አማካሪና የቦርዱ ዋና ጸሀፊ አቶ አፈወርቅ ገ/ፃዲቅ ለሪፖርተር ጋዜጣ ገለጹ፡፡ ረቡዕ ጥር 1 ቀን 2000 ዓ.ም በወጣው ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ..የአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ሶስት ዳይሬክተሮች ከስራ ታገዱ.. በሚል ርዕስ የወጣው ዜናም እንዲስተካከል ሀላፊው ጠይቀዋል፡፡

አቶ አፈወርቅ እንደገለጹት የዶመስቲክ ባንኪንግ ዲፓርትመንት ዳይሬክተር አቶ ከፍያለው ዘገየ፣ የፋይናንስ ዳይሬክተሩ አቶ ገብረ ሚካኤል ታምራት እና የሰው ሀይልና የማዕከላዊ ሰርቪስ ዳይሬክተር አቶ ገብረ እግዚአብሄር ወልዱ ከሀላፊነታቸው የተነሱት ታህሳስ 25 ቀን 2000 ዓ.ም ባቀረቡት መልቀቂያ መሰረት ነው፡፡ ቦርዱም በሀላፊዎቹ ላይ የእገዳ እርምጃ አለመውሰዱን አቶ አፈወርቅ አረጋግጠዋል፡፡

በሌላ በኩል ትናንት በወጣው የእንግሊዝኛው ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ሶስት የአንበሳ ኢንተርናሽናል የቦርድ ዳይሬክተሮች ባቀረቡት መልቀቂያ መሰረት ከሀላፊነታቸው እንደተነሱ ተደርጎ የተዘገበው ስህተት በመሆኑ ..ሶስት የአንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ዳይሬክተሮች.. ተብሎ እንዲስተካከል ከይቅርታ ጋር እንጠይቃለን፡፡

 
< Prev   Next >