Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Thursday
Aug 28th
Home arrow Sections arrow ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ
ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ Print E-mail
Sunday, 13 January 2008
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚዎች መበተናቸውን ያነበብኩት ከሪፖርተር ጋዜጣ ነው፡፡ በዶክተር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ የሚመራው ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ እንዲበተን የተደረገው በጠቅላላ ጉባኤ ነው፡፡

በረቡዕ ታህሳስ 30 ቀን 2000 ዓ.ም ሪፖርተር ጋዜጣ አቶ ጌታቸው ገ/ማሪያም የተባሉት የፌዴሬሽኑ ሥራ አስፈፃሚ ራሳቸውን ከኃላፊነታቸው ማግለላቸውን ሳነብ ገረመኝ፡፡ ከየትኛው ፌዴሬሽን ነው ራሳቸውን ያገለሉት?

ከፈረሰ፣ ታሪኩና ጉዞው ከተደመደመ ፌዴሬሽን እንዴት ራስን ከሥራ ስለማግለል ይወራል፡፡ አቶ ጌታቸው ራሳቸው ከየትኛው ፌዴሬሽን ራስዎትን አገለሉ? ተብለው ቢጠየቁ መልስ የሚሰጡ አይመስለኝም፡፡

ሌላው አቶ ጌታቸው ፃፉት በተባለው ደብዳቤ ከዚህ ቀን ጀምሮ የተወሰነው ውሳኔ አይመለከተኝም ካሉ በኋላ ከሥራ የለቀቁበትን ማመልከቻ ያስገቡበት ቀን በራሱ የተምታታ ነው፡፡

በዚሁ ጋዜጣ አቶ ወርዶፋ በቀለ፣ አቶ አርአያና አቶ አሸናፊ እጅጉ ያቀረቡት መልቀቂያ በጠቅላላ ጉባኤው ተቀባይነት ማግኘቱ አልገባኝም፡፡ ፌዴሬሽኑ ለሠራው በደልና ጥፋት ሁሉም ወገኖች መጠየቅ አለባቸው በሚባልበት በአሁኑ ወቅት የእነሱ መልቀቂያ ተቀባይነት ያገኘው ልክ አቶ ጌታቸው በጉባኤው አካሄድ ላይ ከዶክተር አሸብር ጋር እንዳልተስማሙ "ምንጮች" ገልፀዋል ተብሎ እንደተገለፀው ዓይነት ሆኖብኛል፡፡ ምናለ ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ ዓይነት ጨዋታ ባንጫወት፡፡

(ተክሌ ሲማ፣ ከቦሌ)

 
< Prev   Next >