Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version

Wednesday
Oct 15th
Home arrow Sections arrow ለድሬ አስቸኳይ መፍትሄ
ለድሬ አስቸኳይ መፍትሄ E-mail
Sunday, 13 January 2008

በሪፖርተር ጋዜጣ በልናገር ገጽ ረቡዕ ታህሳስ 30/2000 "ድሬዳዋስ?" በሚል ርዕስ የወጣውን ፅሑፍ አንብቤያለሁ፡፡

በፅሑፉ ላይ የተካተቱ ሐቆች ጥያቄን የሚጭሩ ናቸው፡፡ በሚወራና በሚሠራው መካከል ያለውን ክፍተት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ ፅሑፉ መንግሥትንም የሚያሳስብ ነው፡፡ ከወዲሁ ሳይቃጠል በቅጠል መፍትሄ የሚበጅለት ጉዳይ ነው፡፡

የድሬዳዋ ተደራራቢ ችግሮች አፋጣኝ ምላሽ የሚሹ ናቸው፡፡ በሁሉም የአገሪቱ ክልል ባሉ ከተሞች ያሉ ችግሮች ቀላል ናቸው ማለት ባይቻልም የድሬዳዋ ግን መሠረታዊ ናቸው፡፡ የኦሮሚያና የሶማሌ ክልሎች የይገባናል ጥያቄ ያስከተለው አለመግባባት እስከአሁን ባለመፈታቱ፣ ከተማይቱ ሌሎች ከተሞች ያገኙት ጥቅምና የመሠረተ ልማት አላገኘችም፡፡ በተጨማሪም እስከ አሁን ድንበሯ በውል አለመታወቁ ሌላ ችግር ነው፡፡

በችግር ላይ ችግር እየተደራረበ ለመፍታት እንቅፋት ከመሆኑ በፊት  "የድሬ ነገር" አስቸኳይ መፍትሔ ሊሰጠው ይገባል፡፡

(ተስፋዬ በየነ፣ ከመሿለኪያ)

 
< Prev   Next >