| የምስራቅ ሱዳን ግንባር ልዑካን... |
|
|
| Sunday, 13 January 2008 | |
|
የምስራቅ ሱዳን ግንባር ልዑካን ከኘሬዚዳንት ኢሳያስ ጋር ተወያዩ የኤርትራ ኘሬዚዳንት ከዚህ ቀደም ኤርትራ ስትሸመግልበት የነበረውን ስምምነት ለማፅደቅ ከቀድሞ የምሥራቅ ሱዳን አማፅያን መሪ ጋር ውይይት አደረጉ፡፡ ረቡዕ እለት የሱዳን ኘሬዚደንሻል አማካሪ በሆኑት ሙሳ ሞሀመድ አህመድ ከሚመራው የምስራቅ ሱዳን ግንባር ልዑካን ጋር የተደረገው ውይይት ሁለቱ ፓርቲዎች ጥቅምት አሥራ አራት 2ዐዐ7 ላይ የተደረገው የምስራቅ ሱዳን የሠላም ስምምነት ተግባራዊነት ላይ መነጋገራቸውንና ሁለቱም ፓርቲዎች ስምምነቱን ተፈፃሚ ለማድረግ ቁርጠኝነት ማሳየታቸውን ሻቢትን በመጥቀስ ሱን ትሪቢውን ዘግቧል፡፡ ከካርቱም መንግሥት ጋር በስምምነቱ ተግባራዊነት ላይ በቀጣይነት እንደምትነጋገር ኤርትራ ያስታወቀች ሲሆን የምስራቅ ሱዳን የቀድሞ አማፅያን ግንባር አንድነትን እንዲጠብቁ ጥሪ አስተላልፋለች፡፡ "ስምምነቱ የሚመለከታቸው እያንዳንዱ አካላትን ማጠናከር ለስምምነቱ ተግባራዊነት አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡ የኤርትራና የሱዳን መንግሥታት እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት ለተፈፃሚነቱ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማድረግ ይኖርባቸዋል" ብለዋል፡፡ የምስራቅ ሱዳን ግንባር ልዑካን አስመራ የደረሱት ከኤርትራ መንግሥትና ከገዢው የህግዴፍ በተደረገላቸው ጥሪ መሠረት ነው፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |