Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Jul 20th
Home arrow Sections arrow የሶማልያ ፓርላማ አዲሱን ካቤኔ አፀደቀ
የሶማልያ ፓርላማ አዲሱን ካቤኔ አፀደቀ Print E-mail
Sunday, 13 January 2008
የሶማልያ ፌዴራላዊ የሽግግር ፓርላማ ህግ አውጪዎች በቅርቡ አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኑር አዴ ሁሴን ሀሰን ያቋቋሙትን አዲስ ካቢኔ ማፅደቁ ጋረው ኦንላይን የተባለው ድረ ገፅ ዘገበ፡፡

በባይደዋ ካቢኔውን ለማፅደቅ የተገኙት የምክር ቤት አባላት ቁጥር 230 ነበር፡፡ ከነዚህ ውስጥ በአብላጫ ድምፅ ማለትም 223 የምክር ቤቱ አባላት አዲሱን ካቢኔ አፅድቀውታል፡፡ አምስት የምክር ቤቱ አባላት ካቢኔውን የተቃወሙት ሲሆን 2ቱ ደግሞ ድምፀ ተአቅቦ ማድረጋቸው ምንጮችን ጠቅሶ ድረ ገፁ ገልጿል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ኑር አዴ ከካቤኔው ማፅደቅ በኋላ የመንግሥታቸው ፖሊሲ በብሄራዊ ደህንነት፣ ዕርቅና ለዕርዳታ ሰጪ ድርጅቶች መተባበር በተመለከተ ንግግር ለምክር ቤቱ አቅርበዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ኑር አዴ የመሠረቱት አዲሱ የሶማልያ ካቤኔ 18 አባላት ያቀፈ ሲሆን፣ የሽግግር መንግሥቱ እ.ኤ.አ ከ2ዐዐ4 ጀምሮ እስከ አሁን 31 አባላት ያቀፈ ካቢኔ ነበረው፡፡

አዲሱ ካቢኔ ከሽግግር መንግሥቱ ወጪም አካትቷል፡፡ አዲሱ የኑር አዴ መንግሥት አንዳንድ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል፡፡ ከነዚህ ውስጥ የአገራቱን ደህንነት በተመለከተ፣ በመላ አገሪቱ የፌዴራል ስርዓት መመስረትና አገሪቱን ለመጪው ዓመት ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ማዘጋጀት የመሳሰሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡

በተመሳሳይ የሶማልያ ኘሬዚዳንት አብዱላሂ የሱፍ ጤንነታቸው በደህና ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

 
< Prev   Next >