| በካሊፎርኒያ ድርቅ መግባቱ ተገለፀ |
|
|
| Sunday, 08 June 2008 | |
|
የካሊፎርኒያው ገዢ አርኖልድ ሸዋዚንገር ካለፉት 17 ዓመታት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ግዛቲቱ በድርቅ መመታቷን ይፋ አድርገዋል፡፡
አሶስየሽን ኦፍ ካሊፎርኒያ ወተር ኤጀንሲን ገልፆ ኤስ.ኤፍ.ጌት እንደዘገበው ገዢው ሸዋዚንገር በግዛቲቱ ያለውን የውሃ አጠቃቀም 2ዐ በመቶ ለመቀነስ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ አያይዘውም በአካባቢው የሚገኙ ኤጀንሲዎች የጥበቃ ኘሮግራሞቻቸውን እንዲያጠናክሩና ከፌደራልና ከሌሎች የመንግሥት አካላት ጋር በመተባበር ገበሬዎቻቸውን ከገቡበት የገንዘብ ቀውስ እንዲያወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ "ምንም የምናጠፋው ተጨማሪ ጊዜ የለንም፡፡ ኢኮኖሚያችንን፣ አካባቢያችንንና ደረጃውን የጠበቀ የአኗኗር ዘዴያችንን የሚቀድም ሌላ ጉዳይ የለም" ሲሉ ለችግሩ አፋጣኝ መፍትሄ መሰጠት እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |