| ትኩረት ለባህላዊ የዘመን ቀመሮች |
|
|
| Sunday, 15 June 2008 | |
![]() ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሐቅ አዲስ አበባ በቅርቡ የኢትዮጵያ ሺሕ ዓመት (አምአት) ምክንያት በማድረግ የዓለም ባሕረ ሐሳብ ጉባኤ ማስተናገዷ ይታወሳል፡፡ ከምሥራቁም ሆነ ከምዕራቡ ዓለም እሙራን ሊቃውንት በዘመን አቆጣጠርና በሥነ ፈለክ ዙሪያ ጥናቶቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን በጥንታዊው የኢትዮጵያ አቆጣጠር ባሕረ ሐሳብ ዙሪያም ልዩ ልዩ ሐሳቦች ተስተናብረዋል፡፡ ጉባኤው በዓለም አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያው መሆኑን የተቀረው ዓለም ከስምንት ዓመት በፊት የሚሌኒየሙን መባቻ ሲያከብር እንዳልተካሄደ ያወሱት ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሐቅ ወጣቱ ትውልድ የማንነቱ መለያ በመረዳት እንዲያተኩር ያግዘዋል ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዐውደ ጥናቱ የቀረቡ የጥናት ወረቀቶችና በውይይቱ ሂደት የተነሱ ነጥቦች በስንኝት (ፕሮሲዲንግ) እንደሚያሳትም ይጠበቃል፡፡ የኢትዮጵያን ዘመን አቆጣጠሮች ለማስተዋወቅ መድረኮች ማዘጋጀት አስፈላጊነቱ አያጠያይቅም፡፡ ኢትዮጵያ በውስጧ ባሉት ብሔረሰቦች የተለያዩ ባህላዊ የዘመን አቆጣጠሮች ያሏት በመሆኑ በኅብረተሰቡ ዘንድ እንዲታወቁ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሆነ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን ሁሉን አቀፍ የዘመን አቆጣጠር ጉባኤ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡ የሲዳማ፣ የኦሮሞ፣ የጋምቤላ፣ ወዘተ. ሥርዓቶች ከኢትዮጵያ ሦስተኛው ሺሕ አቀባባል ጋር መከበር ይገባቸዋል፡፡ እምብዛም ትኩረት ባላገኘው የልዩ ልዩ ዘመን አቆጣጠሮች መልኮች በትውልዱ እንዲታወቅ መጪው ትውልድም በዕውቀት ላይ ተመሥርቶ እንዲያከብረው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ድርሻ በከፍተኛ ደረጃ ይጠበቃል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |