|
Sunday, 13 January 2008 |
ማየት የተሳነው ኢትዮጵያዊ ፎቶግራፍ ለሽልማት በቃ ጣሊያናዊው ፎቶ ግራፈር ጊዮቫኒ ማሮዚኒ 11ኛውን ዓለም አቀፍ የሂዩማኒቶሪያን ፎቶግራፍ አዋርድ አሸንፏል፡፡
ፎቶግራፈሩ ለሽልማት የበቃው ..ዘ ኬርስ.. ብሎ የሰየመውና ማየት የተሳነውን ኢትዮጵያዊ ፎቶ ግራፍ አቅርቦ ሲሆን ዓይነ ሥውርነተ በኢትዮጵያ ከባድ ችግር እንደሆነ ጠቁሞ ድህነት፣ የመሠረተ ልማት አለመሟላት፣ ዝቅተኛ የጤና አጠባበቅ ዕውቀት ለችግሩ መንስኤ መሆናቸውን ለመግለፅ ያነሳው ፎቶ ግራፍ መሆኑን አስረድቷል፡፡ በውድድሩ ኬቲ ጐሜዝ በኢንፎርሜሽንና ሰብዓዊ መብት በአውሮፓ ምን እንደሚመስል በማሳየቷ ልዩ ተሸላሚ ሆናለች፡፡ 11ኛው ዓለም አቀፍ የፎቶግራፍ አዋርድ ሩዋንዳ ውስጥ በ1997 የሰብዓዊ ሥራ ለሜዲኮስ ደል ሙንዶ ሲሰራ ህይወቱን ላጣው ፎቶግራፈር ሉዊሳ ቫይልቲየና መታሰቢያነት ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም በሩዋንዳና ቦስኒያ ህይወታቸውን ያጡት የሜዲኮስ ዶል ሙንዶ አባላት ፍሎርስ ሲሬራ ፎርቹኒ፣ ማኑኤል ማድራዞ ኦሲና እና ሜርሲደስ ናቫሮ ሮድሪግዝ ታስበዋል፡፡ |