| ቦክስ ኦፊስ |
|
|
| Wednesday, 18 June 2008 | |
"ዘ ኢንክሪደብል ሁልክ" የተሰኘው ፊልም በአሜሪካ ቦክስ ኦፊስ የመጀመሪያውን ደረጃ እንደያዘ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ፊልሙ በተለቀቀበት በያዘነው ሳምንት 54.5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በመሸጥ ሳምንታዊውን የሰሜን አሜሪካ ቦክስ ኦፊስ ደረጃ በቀዳሚነት ከሚመራው "ዘ ኢንክሪደብል ሁልክ" በማስከተል ሁለተኛ የወጣው "ኩንግ ፉ ፓንዳ" ነው፡፡ ባለፈው ሳምንት የአንደኛ ደረጃነቱን ተቆናጦ የነበረው "ኩንግ ፉ ፓንዳ" 34 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በማስመዝገብ ነው ወደ ሁለተኛነቱ ደረጃ ዝቅ ያለው፡፡ "ዘ ሃፕኒንግ" 30.5 ሚሊዮን ዶላር፣ "ዩ ዶንት ሜስ ዊዝ ዘ ዞሃን" 16.4 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም "ኢንዲያን ጆንስ ኤንድ ዘ ኪንግደም ኦፍ ዘ ክሪስታል ስኩል" 13.5 ሚሊዮን ዶላር በመሸጥ በተከታታይ ከሶስተኛ እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |