Lost Password? No account yet? Register
  • Increase font size
  • Decrease font size
  • Default font size
  • default color
  • red color
  • green color

Reporter - Amharic Version     

Sunday
Sep 07th
Home arrow Sections arrow ኢትዮጵያ ኋላ ቀር አስተራረስዋን...
ኢትዮጵያ ኋላ ቀር አስተራረስዋን... Print E-mail
Sunday, 22 June 2008
ኢትዮጵያ ኋላ ቀር አስተራረስዋን እንድታስተካክል ተጠየቀ

በጋዜጣው ሪፖርተር

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የገጠማትን የምግብ እጥረት ሣቢያ በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝቧ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸውና ይህንን ሁኔታ ለማሻሻልም አገሪቱ ኋላ ቀር የአስተራረስ ዘዴዋን ማስተካከል እንዳለባት የዓለም ባንክ አስታወቀ፡፡
ወቅቱን የጠበቀ ዝናብ ባለመኖሩ ለ4.5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልግ የገለፀው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በምስራቁ የሃገሪቱ ክፍልም የምግብ ዋጋ ንረቱንም መባባሱን ከትናንት በስቲያ የተላለፈው የሮይተርስ ዘገባ ያመለክታል፡፡

በዓለም ባንክ ሲኒየር ቫይስ ኘሬዚዳንትና ዋና ኢኮኖሚስት ጀስቲን ሊን ይፋ እንደሚሉት ..ኢትዮጵያ ባለፉት ሦስትና አራት ዓመታት ተጨባጭ የኢኮኖሚ እድገት አስመዝግባለች፡፡ ይሁንና የተወሰኑ የሃገሪቱ ክፍሎች በሚከተሉት ኋላ ቀር የአስተራረስ ዘዴ ለድርቅ ተጋልጠዋል..

ከሰሀራ በታች ካሉ አገሮች በሕዝብ ብዛቷ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ በከፍተኛ ሁኔታ ችግር ውስጥ ላሉ በተለይም በደቡብና በደቡብ ምሥራቅ አካባቢ ለሚገኙ ሰዎች እርዳታ የሚውል አራት መቶ ሺህ ሜትሪክ ቶን እህል ለመግዛት 325 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚያስፈልጋት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ማስታወቁንም ይኸው የሮይተርስ ዘገባ ያመለክታል፡፡ 85 በመቶ በመሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ 81 ሚሊዮን የሚሆነው ከእጅ ወደ አፍ በሆነ ባህላዊ የአስተራረስ ዘዴ የሚጠቀም በመሆኑ ይህ ሊሻሻል እንደሚገባው ጀስቲን ሊን ይፉ ተናግረዋል፡፡ ..ባለው መልካም የአየር ፀባይ፣ የተለያዩ የተፈጥሮ ሀብቶችና የሰው ኃይል በአገሪቱ ይህ ነው የሚባል ለውጥ ማምጣት አስቸጋሪ ይሆናል ብዬ አላስብም.. በማለትም በኢትዮጵያ ጉዳይ ለሮይተርስ በሰጡት አስተያየት ገልፀዋል፡፡
 
< Prev   Next >