| በላይቤሪያ ሰላም አስከባሪዎች... |
|
|
| Sunday, 13 January 2008 | |
|
በላይቤሪያ ሰላም አስከባሪዎች በሴቶች ላይ የሚያደርሱት ጥቃት ቀነሰ በላይቤሪያ የተባበሩት መንግስታት ሰላም አስከባሪ አባላት በአገሪቱ ሴቶች ላይ የሚፈጽሙትን መሲባዊ ጥቃትና ብዝበዛ በተመለከተ የሚቀርቡ ሪፖርቶች በግማሽ መቀነሳቸውን አፍሮል ኒውስ ዘግቧል፡፡ በቅርቡ የወጣው ሪፖርት በ2006 ወጥቶ ከነበረው የፆታዊ ጥቃት መጠን ጋር በእጅጉ የተለያየ ነው ተብሏል፡፡ የጥቃቱ መቀነስ የሰላም አስከባሪ ልዑክ ሪፖርት በሚደረጉ ጉዳዮች ላይ የሚወስደውን ርምጃ በተመለከተ ይፋ መረጃ የመስጠቱ ውጤት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ልዑኩ ከላይቤሪያ መንግስትና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በመሆን ጥቃቱን ለማስቆም በመሥራቱ እንደሚቀጥል ኃላፊው ሜጀር ጄኔራል ሙሐመድ ጣሂር መግለፃቸውንም ዘገባው አስነብቧል፡፡ ከዚህ ሌላ በሴቶችና በህፃናት ላይ የመፈፀሙ ወሲባዊ ጥቃትና ብዝበዛዎችን በተመለከተ ህዝቡን የማሳወቅ ሥራው እንደሚቀጥል ተጠቁሟል፡፡ |
| < Prev | Next > |
|---|
| Home |
| Sections |
| Forums |
| Reporter - English Ver. |
| Register |
| Contact Us |